Skip to main content

ናዝሬትዬ መሪዎችሽ ለምን ይፈሩሻል?

https://www.facebook.com/twaktola
ናዝሬትዬ መሪዎችሽ ለምን ይፈሩሻል?
ድሮም ጃንሆይ ናዛሬት/አዳማ መምጣት አይወዱም ነበር፣ይባላል፡፡በዚህም የተነሳ ለገላውዴዎስ ት/ቤት መሰረትና ምርቃት ከመምጣታቸው ውጪ ሌላ ጊዜ መች እንደመጡ ሲነገርም አልሰማሁም፡፡መንጌም ሲመጣ በጣም ተደብቆና በድንገት ሲሆን ፣የማስታውሰው ለናዝሬት ቴክኒክ ኮሌጅ (የዛሬው አዳማ ዩኒቨርሲቲ) መሰረትና ምርቃት መምጣቱን ነው፡፡ከዚያ በተረፈ ሁለቱም መሪዎች ወደ ሶደሬ ሲያልፉ ረዥም እድሜ ተመኙ ተብሎ ሕፃናት ወጥተን ቪቫ (VIVA JANHOY! …viva mengistu!..)ብለን እንገባ ነበር፡፡ያኔም ድንገት ካየናቸው ደስታችን ወሰን የለውም ነበር፡፡የልጅ ነገር!ልጅ ሳለሁ እንደ ልጅ እጫወት ነበር …ያለው ማነው?
ታዲያ ፍርሃት የተጋባበት መሌም ናዝሬት መጣ ከተባለ ከተማው በፌደራል ይወረራል፡፡ከዚያ የት እንዳደረ ሳይታወቅ ወይ ምሽቱን ሄዷል ወይ …አድሯል፡፡ካደረ ጎብዟል፡፡ግን መሌ ሶደሬ ሄዶ ያውቃል?….ቢዚ ስለነበር ምስኪን፣….
ግን ግን-ሶስቱም መሪዎችሽ ለምንፈሩሽ- ---እውነት ግን አዳማ/ናዝሬትን ለምን ፈሯት…?
እስቲ እኔ ልገምት፡፡
ጊዜው በጣም ሩቅ ነው ይባላል፡፡ዓጼ ገላውዴዎስ ከግራኝ ጋር ጦርነት ገጥመዋል፡፡ጦርነቱ ተፋፍሞ ዓጼው ብዙ ከገፉ በኋላ ግራኝ ጦሩን አስተባብሮ እየገፋ ይመጣል፡፡ይሄኔ ላለመማረክ ሲዋጉ የነበሩት ንጉስ በስተመጨረሻ ይቆስላሉ በኋላም አሁን ካለው ከዓጼ ገላውዴዎስ ከፍ ብሎ ካለው ከአለሌ ወንዝ ማዶ ባለ ቦታ ተገድለው ተገኙ፡፡በኋላም ግራኝ አንገታቸውን ቆርጦ ወደ ሃረር ወስዶ በግንቡ ላ ሰቀለው የሚል ዲስኩር በገላውዴዎስ ት/ቤት ግቢ ውስጥ በ 50ኛ ዓመት የት/ቤቱ በዓል ላይ ከታወቁ የከተማው ያገር ሽማግሌ ሰምቻለኁ፡፡እንግዲህ የኔ ግምት ከዚህ ንግግር ጋር ይያዛል፡፡
ደም የለመደ አስፋልት ፣ደም የለመደ ሜዳ፣ደም የለመደ…እየተባለ ሲስፈራራ መቼም ሳትሰሙ አትቀሩም ፡፡ እንግዲህ የተራ ሰዎቹ ሳያሆን የታላላቅ መሪዎቻችን የአዳማ ሆነ የናዝሬት ፍርሃት ከዚህ የሚመነጭ ይመስለኛል፡፡ካልሆነ ከምን ሊሆን ይችላል;…ነው ወይስ ከጥላቻ;….በእርግጥ ናዝሬቶች በጋራ በተከበበች ከተማችን የማይበጀንን መውጫ ማሳጣቱን እናውቅበታለን፡፡ካልሆነ እርም ብሎ ይወጣታል እንጂ በቀላሉ አንለቀውም፡፡ለዚህም ይሆናል በጥቂት አመታት ውስጥ ብቻ ከ14 በላ ይ ከንቲባ ሲመጣና ሲባረር የታየባት፡፡አይመቹንም እኛም አንመቻቸውም ፡፡ታዲያ እኮ ምናለ ቢተውን !...አሊያም የራሳችንነ ከንቲባ ራሳችን እንድንመርጥ ነፃነታችንን ቢመልሱልን፡፡
በመጨረሻ አንድ ቀልድ ቢጤ ልንገራችሁ፡፡
ሙስና የማይቀበል ከንቲባ መጣላት ተባለና 6 ወር ሙሉ ተወራ፡፡ያ ሰው የ6ወር ሪፖርት በግልፅ ሊያሰማና ከህዝቡ አስተያየት ሊሰበስብ በተንጣለለው የኦሊያድ አዳራሽ ኅዝቡን ያወያያል፡፡በከተማው ስላለው ጃንሆይ ስላሰሩት ሆስፒታል እየተወራ ነው፡፡እሱ የአዳማ ሆስፒታል እያለ ያትታል፡፡ ህዝቡ ደሞ የኀይለ ማርያም ማሞ ሆ/ል እያለ ችግሩን ይገልፃል፡፡በኋላ ሰብሳቢው አዲሱ ከንቲባ ግራ እንደተጋባ በሚገልጽ ሁኔታ ሆኖ ሲቆጣ ማዳመጥ ጀመረ፡፡ “አንዴ ቆይ እስቲ እኔ የማወራው እኮ ስለ አዳማ ሆ/ል ነው የትኛወ ነው ኀይለማርያም ማሞ ሆ/ል”?.. ብሎ ቁጭ!.....የተሰበሰበው ሕዝብ ሳቀበት፡፡በሆታም የቀድሞ ስሙ ኃይለ-ማሪያም ማሞ መሆኑን ሕዝቡ ነገረው፡፡
ይህ ሰው ማ መሰላችሁ?>>>፣በቅርቡ በታማኝነቱ በፈንጂ ወረዳ ላይ የተመደበው -መላኩ ፈንታን ቀይሮ በግራ ተመላላሽ መስመር ላይ በአጥቂነት የሚጫወተው በከር ሻሌ ነው፡፡አሪፍ ነበር ይላሉ ፣አንዳንድ የአዳማ ነዋሪዎች በቁጭት፡፡ሳንጠቀምብት ተነጠቅን !... አንዳንዶች ውስጥ አዋቂዎች እንደሚሉት ሰውዬውን ለማስመለስ ሰልፍ ቢጤ የጠየቁ ሰዎች በመሃል አዳማ በየቀኑ በህቡዕ ፖሰታ ቤት አካባቢ ፈረንጆቹ ሲት ኢን(sit-in) የሚሉትን የሰላማዊ ተቃውሞ እያደረጉ መሆኑን ሲናገሩ ሰምቻለሁ፡፡ሰዎቹ ከንቲባችን ካልተመለሰ አንነሳም ድዳችንን ማስጣት ማንም አይከለክለንም-በገዛ ድድ ማስጫችን ማን ይከለክለናል ብለዋል፣ብለው ሲያወሩ ሰምቻለሁ ብሎ ነግሮኛል፡፡ካላመናችሁ ፖስታ ቤት አካባቢ ሂዱና እዩ…በዕርግጥ መፈክር አይዙም…በህቡዕ የሚደረግ ሰልፍ ነዋ…አችሉም እንዴ!
ናዝሬትዬ አትፍሩኝ በያቸው በናትሽ፣ግፋ ቢል ቀጨማ ነው!.....ግፋ ቢል አዱላላ ነው!.....ግፋ ቢል ሙክዬ ነው!...እነሆ አሁን ደግሞ መሪዎቿ በሚፈሯት ኣደማ/ናዘሬት የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ፅ/ቤትን ለመክፈት ተቸግረናል፡፡አንድነቶችጰዋጉሜ 3/2005ዓ/ም ባደረጉት የተቃውሞ ሰልፍ አስፈሪነታቸውን አሳዩ መሰለኝ ይኸው ዳፋው ለኛ ደረስን፡፡እሺ ከፍርኃት ሚገላግል ምን ይምጣ….አሃ!...ለምን እኛም እዛ ድድ ማስጫላይ ሲት ኢን አናደርግም….በቃ አደባባዩ ላይ እንገናኝ፡፡አደባባይ ማከራየት ተጀምሮ ይሆንደሞ እንዴ… ተከራይተንም ቢሆን ድምፃችንን ማሰማታችን አይቀርም፡፡
ተገናኘን ፡፡እንበርታ አቦ!

Comments

Popular posts from this blog

የወሲብ ግፍና ዘመን

(This post had been on my other blog since April 04,2013. Please consider the original post date while reading.) ዘመነ ወሲብ ዛሬ ዛሬ መቼም ትዳር የሚባለው ጎጆ የጋብቻ   ምሰጢር ያለበት አልመስል ብሏል፡፡ በአፀያፊ መልኩ ዎንዶችና ሴቶች ገና ጨቅላ በሚባል የጉልምስና (በዘመንኛው ቃል የፍንዳታ እድሜ ይሉታል፡፡) እድሜያቸው ወሲብ መጀመራቸውና በአስራዎቹ አጋማሽ ላይ ሲደርሱ ዓለም ሰየጠንሁ  ያለበትን የወሲብ ክህሎት ጣራ ነክተው ከዚያ ሲዳክሩ ይከረሙና በወላጅ ይሁን በኑሮ ግፊት ትዳር ይመሰርታሉ፡፡ የዚህ አዲስ አይነት ጎጆ አባላት ደግሞ በአብዛኛው የሚያስቁ ጥነዶች የሆናሉ፡፡ እነዲህ ያለው ትዳር የተመሰረተው ለገንዘብ ወይም ለውጭ ሀገር ዕድል ከሆነ፤ ተጋቢዎቹም ሆነ ገገባው ሩቅ ሳይሄድ ህጋዊ ፍች እንደሚፈፀምበት ገና የሰርጉ እለት ያውቁታል፡፡ በቤተሰብ ግፊትና በአብሮ አበዶች ሆይሆይታ የሚቀለስም ተመሳሳይ ጎጆ አለ፡፡ ብቻ ይህኛውም መቼ  እነደሚሆን አይታወቅም እንጂ ላይዘልቅ እንደሚችል ተጋቢዎቹም ሆኑ እኛ ስለጋብቻው አሁን የሰማን ሰዎች ከልምዳችን በመነሳት እርግጠኞች መሆን ንችላለን፡፡ የሆኖሆኖ የዛሬ ትዳር ምነም እክሎችን የያዘ እነደሆነ ላሰታውሳችሁ፡፡ ውሽምና ድጋፍ ባያገኝም አስከዚህኛው ትውልድ በመዝለቁ፤ ወደሽርሙጥና  እና  የዳማ በሚል ስያሜ በቡድን ለሚፈፀም ሰው ሰራሽ አረመኔያዊ ወሲብነት አድጓ፡፡ ጥነዶች በአንድ ጣራ ስር ሆነው እንኳ በተመሳሳይ ሰዓት ከተለያዩ ሰዎች ጋር በስልክ ወሲብ ራሳቸውን ያረካሉ፡፡ የነውሩ ዘመን   በአባቶቻችንና ከዚያ ቀደም ባለው ትውልድ ወሲብ በይፋ በየመንገዱ እንደልብ የሚወሳ ሳይሆን እንደነውር ...

Hino da Etiópia (voz) Ethiopia National Anthem (vocal) (source: http://s.ytimg.com)

የሷ ሱስ

የወደዷትን ልጅ እያወዳደሱ እያሞጋገሱ እንዲህ እያስደነሱ፤ ልፍታ ልተው ቢሏት እንኳንስ ፍቅሯና አይለቅህም ሱሱ! tsenawoo