Skip to main content

Posts

Showing posts from December 16, 2013

ሃገሬ አህያ ናት!

  ትንፋሽ አሳጥቶ በርሃብ ቀጥቶ ጉልበቷ እስከሚዝል በዝቶብኛል ሳትል ተራራ ሜዳውን ማንም የሚነዳት አንዱ ሲጋልባት ሌላው የሚጭናት ሃገሬ አህያ ናት! ክብሯ የትም ወድቆ መብቷ ተንቆ ጅራፍና ዱላው ሲፈራረቁባት ነይ ወደዚህ ሲሏት ሂጅ ወደዚያ ሲሏት ሃገሬ የእኔ እናት የመሪዎች ሸክም ወገቧን አጉብጧት እንደማሽላ አራ ደግሞም እየሳቀች   በዘመን ፋርጎ ላይ ዛሬም ትጏዛለች! Source (የግጥም ምሽት በፌስቡክ) //በዘሐዲስ አየለ//