Skip to main content

Posts

Showing posts from 2023

ለመሆኑ በግንቦት 20 ነፃነት የታወጅው ለማን ነው?

Note: - posted date: June 01, 2018.            - I found this as a draft on my blog and regretted not posting it on time, it was written 4 years ago. Now: re-posted here because I am cleaning my other blog. ለመሆኑ በግንቦት 20 ነፃነት የታወጅው ለማን ነው? ለራስ ወዳድ እና ለዝራፊ ዘርኞችና ተከታዮቻቸው ይሆን? ለማንኛውም የጠብ መንጃ የእርስ በእርስ ጦርነት እነዲቆም የታወጀበት ቀን ተብሎ ቢሰኝ ኖሮ ያለጥርጥር ከአድዋ እኩል ክብር የሚያሰጥ ይሆን ነበር፡፡  ያለመታደል ሆኖ መሪዎቻችን ትናንትን ብቻ በማነፃፀር በጎ የሰሩ እነዲመስል የሚያደርጉት ጥረት ውጤቱ ሆዳቸውን ለማስፋት ነውና ለምስኪኑ ዜጋ እኔ በግሌ ምንም ማድረግ ያለመቻሌ ሁልጊዜም ያንገበግበኛል፡፡ ስንት ሆዳሞችን እያበረታቱ ሀገሪቱን ራቁቷን ለማስቀረት ከጣሩ ሆዳም መሪዎች መካከል አቶ መለስን ለየት የሚያደርጋቸው ነገር ቢኖር፣ በዘር እና በሃይማኖት ሽፋን ሀገራችን ኢትዮጲያን ከአንድነት ወደ መበታተን ለማድረግ ያደረጉት ጥረት ብቻ ነው፡፡  ደግነቱ የኢትዮጲያ ህዝብ ፎረሙላ እና ቀመር እንኳን ለ አምባገነን መሪዎቿ ይቅርና በፀሎት ተጋን ለሚሉትም ምስጢር ሆኖባቸው ዘመናት ተቆጥረዋል፡፡

I don' exactly seem to understand what's going on evrey corner of `Woreda` governance!

(This post had been originally found on my other blog since April 03, 2014. Please consider the date while reading.) late yesterday, a man in a local Kebele, old K-12, in Nazareth, Ethiopia broken in to a house who he called is owned by an ethnic member_ not from his, saying that the men in the house don't belong in there!  Perhaps his better-settled bosses showed him to trick owners by force in public; however, it seems didn't work this time. Yet the questions continue in the minds of the town people! (the walls were down by the conquering man)

Voice of Africa; empowering self esteem

(This post had been originally found on my other blog since May 25, 2013. Please consider post date while reading.)              As dreamed to have achieved the greatness of Africa every nation shall take part an adhesive self development of thinking, working, saving and serving. No desperate movement of individual, small group and, or clan interest shall be recorded in the coming Africa. African shall learn to really stand together.  Since the beginning, all the world noted    how potentially resourceful Africa was. The strong power of the western interest scrambled the continent for years and had employed varies tying techniques to lame the nation so that the invaders keep on sipping raw materials and human resources. As far as most African countries are concerned, ethnicity and poor administration have been playing a vital role in the sluggish growth of the continent in contrary to the fast emerging new technologies and understanding of human rights. Civil war and corruption have be

Know well, fair

(This Post had been originally found on y other blog since  April 21, 2013. Please consider post date while reading.) First Afro-American president in the USA; the only uncolonized African country; first Olympic medalist to Ethiopia; first man to moon; Adolf Hitler; Nelson Mandela; Prophet Mohammed; Jesus Christ and a lot more are known to man with tangible evidence. Plenty of matters win an issue in to our sentimental heart. Surely every one dreamed to have done one of such prominent story to be added in to the story book of the world. Besides the strong will of each code in the mind of thirsty nation, the most commonly convincing point boarding the world is the expressive existence of truth that never changes.    No part of rightly written history changes, but the writer and the way it is written does. Enormous amount of qualities and standards we quote never disagree with the world outside since we have the right references.  Institutionalized schools and research centers have been

አስተያየት ነውር ነውን? (Is a comment a taboo?)

(This post had been originally found on my other blog since  April 14, 2013. Please consider the original date while reading.) ስነ ሂስ ለለውጥ መርሃ ግብር መሰረታዊ አስተዋፅዖ ስለማድረጉ የጠቢባን እምነት ነው፡፡ ጠቢባንም የልፋታቸው ሚሰጥር ስለጥበብ ቋንቋና ምግባር እድገት ነው፡፡ በመሆኑም ጠቢባን ጥበበኛ የሚባሉት ባበረከቱት መሰረታዊና መደበኛ ያልሆኑ መልካም አስተዋፅዖዎች ነው፡፡ የፖለቲካ አመለካከት ቅኝት ከማጣቱ የተነሳ በእውቀት ማነስ ከሚወቃቀሱ፣ ከሚነካከሱ እና ከሚገዳደሉ የህዝብ አካላት ተፅዕኖ ምክኒትያት ሂስ መስጠትም ሆነ ግድፈትን ማውራት የተቃዋሚ ወይም ተፃራሪ ቦታን ስለሚያሰጥ ጤናማ የሚባል ወይም ለዕድገት የጋራ ሚና ያለው አስተያየት ማግኘት የለም፡፡ እሳት ወለደች አይነት ነው፡፡ ስለሆነነም ስለመፃህፍት፣ አስተምህሮ፣ የስልጠና ማዕከላት፣ የሆቴልና ቱሪዝም አገልግሎት፣ ወዘተ ባነሳን ቁጥር ስለዕድገትና ብልፅግና እያሰቡ ጉድለቶችን አንስቶ መተቸት ወይም ስህተቶችን መወረፍ እጅግ ነውረኛነትና “ከመልካም አሳቢው” ባለመፅሃፍ፣ አስተማሪ፣ የስልጠና ባለሙያ አልያም የሆቴልና ቱሪዝም አገልጋይ ዘንድ ጠላት ሆነኖ የመፈረጅን እድል ያጋፍጣል፡፡ ከዚህም ጋር ተያይዞ በሃገራችን እንጭጭ ሊባል የሚችል እድሜና እምብዛም አልተመደበለትም ሊባል የሚያስችል የገንዘብ በጀት የተደረገበትን የፊልም ጥበብን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሚቀርብበትን ትችት በመመርኮዝ ባለሙያዎችና ባለሃብቱ ጥለውት እየፈረጠጡ፤ መንግስትም በግብርና ተዛማጅ ማነቆ ጣጣዎች ከፍተኛ ጫና በማድረግ ስለጥበቡ መሻሻል ግድፈቶች እንዲሻሻሉ የጠቆሙ ሂሰኞችን ለማሳፈር በሚመስል አካሄድ ለዘርፉ ማደግ የራሳቸውን የእንቅፋትነት ድርሻ አየተወጡ ይገ

ልፋ ያለው በሬ ቆዳው ከበሮ ይወጠራል!

(This Post had been originally posted on my other blog on April 16, 2013. Please consider the post date while reading.) ይህ ፅሁፍ በ October 29, 2011 ለአዲስ ጉዳይ መፅሄት ተልኮ የነበረ ሲሆን አንዳንድ እርማት ተደርጎለት እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡ወቅቱ በመፅሄቷ ላይ “ኩበት በሌለበት ጭስ ከየት ይመጣል?” በሚል ርዕስ የሀገራችንን የፊለም ንግድ (ይቅርታ የፊልም ጥበብ ለማለት ተሳቅቄ ነው፡፡) በመውቀስ ለዘርፉ ያለውን ወዳጅነት አሳይቶ ለሌሎች ታዳሚዎችም ጋብዞ ተሰናብቶ ነበር፡፡ እስቲ እኔም እኛ ተመልካቾች ስለማረራችን ትንሽ ልክተብ ብዬ ተነሳሁ፡፡ አሁን ዘመኑ አለማቀፋዊነት እየገነነ የመጣበትና በየሀገሩ ጫፍና ጫፍ እየጠፋ፣ ሁሉም ከተሜ እየሆነ፣ መረጃ ሙሉ በሙሉ እየተዳረሰ፣ በሰከንዶች ልዩነት ድምፅና ምስልን ያቀናበሩ ወሬዎች በየርዕሰ ጉዳዩ    ለጆሮና ለአይን    ሲበቁ ማስተዋል እነኳን ጥበብን ለሚናፍቁና ጠቢባን ነን ለሚሉ ቀርቶ ለእንደኔ ላለውም ተራ ግለሰብ አንዳች መንገድ ይጠቁማል ባይ ነኝ፡፡ ምንም እንኳ ትምህርቴ ያልገፋና በአንድም ዘርስ ተሳክቶልኝ በቴሌቪዥን፣ በሬዲዮ፣ በጋዜጦችና በመፅሄቶች ለህዝብ እይታና    ጆሮ የቀረበረሁ ሰው ባልሆንም አልፎ አልፎም ቢሆን ስለጥበብ የተፃፉ ፅሁፎችን የማንበብንና ሲተረኩ የመስማት ዕድል ገጥሞኛል፡፡ ይህም ዕድል ለብዙዎች የተነፈገ ስላይደለ የምሰጠው አስተያየትም በተራው ታዳሚና ተመመልካች አናሳ እውቀት ላይ መሰረት ያደረገ ነው ማለት ነው፡፡ ጥበብን በርካታ ጠቢባን እያሞካሹና እያወደሱ ረቀቅ ያለ ትርጓሜ እንደ ሚሰጧት እኔ ብናገር ለቀባሪው ማርዳት ይሆንብኛል፡፡ ጠቢባንን    ግን ወረፍ ማድረግ ለእውቅናቸውና እውቀታቸው ተጨማሪ ግብዓት

Sometimes ...

  Sometimes days come to tell how we really feel about ourselves or whether we are confused. But what we speak or write is meaningful to others too. Does any one of this mean something to you?

የወሲብ ግፍና ዘመን

(This post had been on my other blog since April 04,2013. Please consider the original post date while reading.) ዘመነ ወሲብ ዛሬ ዛሬ መቼም ትዳር የሚባለው ጎጆ የጋብቻ   ምሰጢር ያለበት አልመስል ብሏል፡፡ በአፀያፊ መልኩ ዎንዶችና ሴቶች ገና ጨቅላ በሚባል የጉልምስና (በዘመንኛው ቃል የፍንዳታ እድሜ ይሉታል፡፡) እድሜያቸው ወሲብ መጀመራቸውና በአስራዎቹ አጋማሽ ላይ ሲደርሱ ዓለም ሰየጠንሁ  ያለበትን የወሲብ ክህሎት ጣራ ነክተው ከዚያ ሲዳክሩ ይከረሙና በወላጅ ይሁን በኑሮ ግፊት ትዳር ይመሰርታሉ፡፡ የዚህ አዲስ አይነት ጎጆ አባላት ደግሞ በአብዛኛው የሚያስቁ ጥነዶች የሆናሉ፡፡ እነዲህ ያለው ትዳር የተመሰረተው ለገንዘብ ወይም ለውጭ ሀገር ዕድል ከሆነ፤ ተጋቢዎቹም ሆነ ገገባው ሩቅ ሳይሄድ ህጋዊ ፍች እንደሚፈፀምበት ገና የሰርጉ እለት ያውቁታል፡፡ በቤተሰብ ግፊትና በአብሮ አበዶች ሆይሆይታ የሚቀለስም ተመሳሳይ ጎጆ አለ፡፡ ብቻ ይህኛውም መቼ  እነደሚሆን አይታወቅም እንጂ ላይዘልቅ እንደሚችል ተጋቢዎቹም ሆኑ እኛ ስለጋብቻው አሁን የሰማን ሰዎች ከልምዳችን በመነሳት እርግጠኞች መሆን ንችላለን፡፡ የሆኖሆኖ የዛሬ ትዳር ምነም እክሎችን የያዘ እነደሆነ ላሰታውሳችሁ፡፡ ውሽምና ድጋፍ ባያገኝም አስከዚህኛው ትውልድ በመዝለቁ፤ ወደሽርሙጥና  እና  የዳማ በሚል ስያሜ በቡድን ለሚፈፀም ሰው ሰራሽ አረመኔያዊ ወሲብነት አድጓ፡፡ ጥነዶች በአንድ ጣራ ስር ሆነው እንኳ በተመሳሳይ ሰዓት ከተለያዩ ሰዎች ጋር በስልክ ወሲብ ራሳቸውን ያረካሉ፡፡ የነውሩ ዘመን   በአባቶቻችንና ከዚያ ቀደም ባለው ትውልድ ወሲብ በይፋ በየመንገዱ እንደልብ የሚወሳ ሳይሆን እንደነውር ተሸሽጎ የተያዘ ቢመስልም ዛሬ እውነቱን ለማስተዋል እንገደዳለን

Wish a real election

(This post had been posted on  April 02, 2013 on my other blog. Please consider the original date while reading.) As man wishes to show progress in his future career, he in the beginning manages to think through every possible step and follow them to prove his development. For no question each individual in a country counts everything passing by, the short of money, illiteracy and wise governance. No matter most African countries still promote scarcity evoking unfair resolution of life standard among the nation. Ethiopia, likewise, has been proceeding with the same technique. Corrupted and autocratic leaders still hold the position.    Though visible progress the development program is undeniable, the government has to show on more tangible backing of the citizen benefit in every pace.  Smuggling money, raw material, weapon, drug and clothing are still in high contribution to the unstable market in the country. Officially registered traders are mostly running their mixed business, the

የመለስ ፋውነዴሽን (Meles Foundation)

(This post had been originally posted on April 03,2013 on my other blog please consider the original date) በርካታ ባህላዊና ዘመናዊ መንግስታትን ያለ ግልፅ ቅኝ ተገዢነት ያስተናገደችው ሀገራችን ከጊዜ ወደ ጊዜ የመልካም አስተዳደር እጦትና የሰበዓዊ መብት ረገጣ እየተባባሰ በመምጣቱ ሳቢያ ሕዝቡ የዜግነት መብቱን በመንግስት ስልጣን ላይ ባሉ ግለሰቦች ወይንም ቡድኖች ፈቃድ ብቻ ሊሰጠው ወይም ሊነፈገው የሚችል መሆኑን እያመነ መጥቷል፡፡ ይባስ ብሎ መንግስት ለሕዝቡ ጥቅም በሚል በሚዘረጋቸው በማንኛውም የልማት መርሀ ግብሮች የመንግስትንና የግል ሌቦችን በሚያበረታታ መልኩ በዘፈቀደ አሰራር እየተሰራ ነገር ግን ለይስሙላ ያህል የሒሳብና የሚዲያ ሪፖርቶች እንደሚደረጉ ያደባባይ ሚስጥር ከሆነ እየሰነበተ ነው፡፡ የሆኖ ሆኖ ለሃያ አመታት፤ ሊያውም በዚህ በዘመነ ግሎባላይዜሽን ሀገራችንን በስልጣን ሲያስተዳድር የቆየው ኢሕአዴግ ከስልጣን ጊዜው ቀድሞ የክፉውን ጨለማ ሳይቀር አሸንፎ የመጣለትን ጠንካራ (በእኔ አተያይ አስሊ እና ከዱረዬ ባልተናነሰ በፈንግጪው ውጤት ተኮር) የሆነ መሪውን ካጣ ይኸው መንፈቅ ሞላው፡፡ ያለአንድ አምባገነን ምልክትነት ሕዝቡን ሰቅዞ ይዞ መምራት ያለመደበት የኢትዮጲያ መንግስት አገዛዝ ቀጣዩን መሪ አይነኬ አድርጎ በህዝቡ ላይ ለመሳል ተስኖት እየተውተተረተረ ይገኛል፡፡ ይህ በእንዲህ እነዳለም የመለስን ፋውነዴሽን ለማቋቋም ጥረቱ ቀጠሎ በመጪው ቅዳሜ በይፋ ፀድቆ ስራ ይጀምራል፡፡ የቅርቡን ቢልከሊነተንን ጨምሮ በርካታ የዓለም ሀገራት መሪዎች፤ ታዋቂ አረቲሰቶችና በየተለያዩ ስራቸው እውቅናና ሀብትን ያተረፉ የየዘርፉ ባለሙያዎች ራሳቸው እነደ አምባሳደር በመሆነን በርካታ የበጎ ፈቃድ ስራዎችን የሚሰሩ ድ