Skip to main content

Posts

Showing posts from 2014

ቀልድ ስላለማወቃችን

12/11/2006EC አንድ ሰሞን ወደሁለት ተከፍላ ብዙም ሳትቆይ እርስ በእርስ ጦርነት ውስጥ የገባችው ሱዳን የገጠማትን ምስቅልቅል ሁኔታ ለመከታተል አለም ሁሉ ጆሮውን አቁሞ ነበረ፡፡ ቀድሞም ጠግቦ ያላደረው ደሃ ሕዝብ ነፍሱን ስለማቆየት ሲል ወደጎረቤት ሀገራት ተሰዷል፡፡ በዛ አስቸጋሪ ወቅት ግን አቶ ሳልቫኪየር ከየሀገራቸው እድገትና ስልጣኔ ያልተመጣጠነ ምቾት ስላሰከራቸው አቻዎቻቸው ጉዳይ እንጂ ስለ ሕዝባቸው ፈፅሞ ግድ የሌላቸው እንደሆነ መሰከሩልን፡፡ “የፀጥታውን ስምምነት የፈረምኩት የኢትዮጲያው ጠቅላይ ሚኒሰተር አስርሃለሁ ስላሉኝ ነው”-ብለው አስደመሙን፡፡  ጋዜጠኞቹም ለጉዳዩ መልስ ሲጠባበቁ ቆዩና ሰሞኑን አቶ ኃይለማሪያምን ማብራሪያ ይጠይቋቸዋል፡፡ እርሳቸውም ሳልቫኪየር ቀልዴን ነው ብለዋል ሲሉ መለሱ፡፡ እንዲያውም እነዚህ ጋዜጠኞች ቀልድ አያውቁም ብለው መናገራቸውን ሊያብራሩ ሞክረው አለፉ፡፡ ይህም የአቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ደረቅ ቀልድ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ ኢቴቪ 1 ፣ 2 ፣ 3 ፣ 4 ተብሎ ይቀለዳል፤ ስለመብራት ስርጭት ብዙ ቁም ነገር የሚመስሉ ቀልዶች እንሰማለን፤ እናያለን፡፡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የትምህርት ጥራት ላይ በተጠናከረ መልክ እየሰሩ መሆኑን ይነግሩናል__የቀልዳቸውን፡፡ መንግስት ጸረ - ሰላም ሀይሎች የህዝብን ጥቅም የሚነኩ ኢ - ሰብዐዊ ድርጊቶችን ለመፈጸም ሲያሴሩ ደርሼባቸዋለው ብሎ የቀልዱን ይነግረንና አሴሩ የተባሉትን አሳራቸውን ያበላቸዋል፤ግን የቀልዱን ነው፡፡የሃገሪቷን ሰላም ለማደፍረስ ስለመነሳታቸው መረጃ የለማ ! ቀላል የከተማ ባቡር መጓጓዣን ስራ ለማሰጀመር ሩጫው እየተፋጠነ መሆኑ በተደጋጋሚ በቴሌቪዥን

ፖለቲኳስ ቢሆን...!

                                                                                                                                      19/10/2006 ኳስ ክብ መሆኗ ብቻ ለአለም መነጋገሪያ አላደረጋትም፡፡ በእግር መለወሷም ከቶ አላስናቃትም፡፡ ብዙ ሚሊዮኖችን ታስፈነጥዛለች፤ ብዙ ሚሊዮኖችን ታስመነዝራለች፤ ለብዙ ሚሊዮኖች የስራ እድል ፈጥራ እንጀራ ታበላለች፡፡ ሊያውም “fair play” የሚል የሚዛንን አድልዎ የሚኮንን መፈክር አንግባ! ይልቁንም አለሙን ሁሉ በአንድ ቋንቋ ታዘምራለች፡፡ የግል ብቃትና ልዩ ክህሎት፣የቡድን ስራ እና ቁርጠኛ አመራር፣ የላቀ አፈፃፀም ያለውን ጠንካራ ቡድን ይመሰርታሉ፡፡ ምግብ፣ አልባስ፣ እና መጠለያ፤ የጤና ባለሙያ፣ የስነልቦና አማካሪ፣ ወኔ ወስቃሽ እና ሌሎች ሁሉ ስለ ቡድኑ ውጤት የበኩላቸውን አስተዋፅዖ እረገው በሚመዘገበው ድል ይረካሉ፣ ይቦርቃሉ፡፡ እንኳንና እነሱ ደጋፊዎች በሩቅ ሆነው እርሳቸውን እስኪስቱ   ይደሰታሉ፤ ስለ ድሉ ይዘምራሉ፤ በየቅፅበቱ በሚፈጠሩ ሁኔታዎች ሁሉ በጉጉት ይወራጫሉ፤ በቁጭት ይንገበገባሉ፡፡ ይህ ሁሉ የሚሆነው ግን   ኳስ ገደብ ስላላት፣ እንዲሁም የተጫዋች ቅያሬ ልክ፤ የመለዮ ልብስ አግባብ፤ የግብ ሁኔታ፤ የመከላከልና የአፀፋ ምላሽ፤ ዝላይ፣ መንሸራተት፣ የእጅ ጣልቃ ገብነት፤ የማንቂያ ደውል(ፊሽካ፤) … ብቻ ሁሉም ገደብ አለው፡፡ እነዚህ ገደቦቸች ቢጣሱ የሚያስከትሉት ቅጣት አለ፡፡ ገደቦቹም ሆነ ቅጣቶቹ ለሕዝብ በማያሻማ መልኩ ይቀመጣሉ፡፡ በየደረጃውም በሰፈር ጨዋታዎች ሳይቀሩ ይተገበራሉየበላይ    ጠባቂም አላቸው፡፡ እነርሱም የሚየሻሙ ነጥቦችን ከዘመኑ ጋር እየዘመነ በሚሄደው ቴክኖሎጂ ሳይቀር እየታገዙ

I am an Oromo too! ስለምን ይዘበትብናል…?

እኛ በሰው አምሳል መፈጠራችንንና ከናንተው እኩል የሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ሰዎች ስለመሆናችን እንዴት ተዘነጋችሁ! ቀደምት አባቶቻችን ስንቶቹን ደራሽ ያጡ የሀገራችንን ኢትዮጲያ ልጆች ጡት እያጠቡ ከአብራካቸው ከወጡ ልጆቻቸው እኩል እያስተማሩና ሀብት ንብረት እያወረሱ ለወግ ማዕረግ ያበቁ መሆናቸው ተረሳችሁ…? ኢትዮጲያዊነትን ከኦሮሞ ሕዝብ፤ የኦሮሞን ህዝብ ከኢትዮጲያዊነት በመነጣጠል የምታገኙት ልዩ ጥቅም እነደሚኖር ሳይታለም የተፈታ መሆኑ በየጓዳው የሚወራው ለዚህም አይደል ብላችሁ እነዴት አልጠረጠራችሁም…? ሕዝቡ ሁሉ ተጠርጣሪ (ሊያውም በሽብርተኝነት) ተብሎ በይፋ እስር ቤት   እንዲገባ የሚቻላችሁ መስሏችሁ ይሆን…? እንኪያስ የትኛውን ሕዝብ ልትመሩት ነው…?(ይቅርታ በአይንህን ጨፍን ላሞኝህ ልትነግዱበት ነው…?- ለማለት ፈልጌ ነው፡፡) ለነገሩ ዞን 9ኞችን የመፍጠሩ ስትራቴጂ ሲነቃባችሁ ዞን 9 ነዋሪውን ትታችሁ ብሎገሮቹን ታስሩ ታንገላቱ ታሳድዱ ዘንድስ ማን አይዟችሁ እንዳላችሁ ምን ይታወቃል…? ይህች ፅሁፍ እንኳ ካቅሟ በመንግስታችሁ እውቅና አግኝታ ከመነበብና የፀሃፊውን መብት ከማስከበር ትታገድ ይሆናል፡፡ ማን ያውቃል…? ዓለም ሁሉ በንግድ /ቢዝነስ/ ፅንሰ ሃሳብ በተወጠረችበት በዚህ ዘመን የኋሊዮሽ የተንቋሸሸሽንበት ያህል እንዲሰማን የተደረግንባቸውን የሀገራችንን ታሪክ እየባዘታችሁ ስለምን የትውልዱን ተስፋ በቁንፅል ሃሳብ በመወጠር ትቀጩብናላችሁ…? እናንተ የምትገነቡትን ሕንፃ፣ ለሎችን በመጨቆን ስንጥቅ የምታተርፉበትን ንግድ፣ በሀሰት ህዝብን እየሸነገላችሁ የምትቸበችቡትን መሬት፣ የምታቀያይሯቸውን መኪኖች፣ ህዝብ የሚያውቃቸውና የማያውቃቸው በአጭር ጊዜ የምትበለፅጉባቻው መንገዶች ሁሉ ከዓይንና ከህሊናችን የተሰወሩ ይመስላችሁ ይሆን…?

Art for change!

Dr. Dagnachew Assefa is coming to Nazareth/Adama to meet freedom learners; his philosophical views would be on the panelist's live stage at Tokuma Hotel.

ናዝሬትዬ መሪዎችሽ ለምን ይፈሩሻል?

Tesfaye Waktola https://www.facebook.com/twaktola Andinet Ada-nazreth ናዝሬትዬ መሪዎችሽ ለምን ይፈሩሻል? ድሮም ጃንሆይ ናዛሬት/አዳማ መምጣት አይወዱም ነበር፣ይባላል፡፡በዚህም የተነሳ ለገላውዴዎስ ት/ቤት መሰረትና ምርቃት ከመምጣታቸው ውጪ ሌላ ጊዜ መች እንደመጡ ሲነገርም አልሰማሁም፡፡መንጌም ሲመጣ በጣም ተደብቆና በድንገት ሲሆን ፣የማስታውሰው ለናዝሬት ቴክኒክ ኮሌጅ (የዛሬው አዳማ ዩኒቨርሲቲ) መሰረትና ምርቃት መምጣቱን ነው፡፡ከዚያ በተረፈ ሁለቱም መሪዎች ወደ ሶደሬ ሲያልፉ ረዥም እድሜ ተመኙ ተብሎ ሕፃናት ወጥተን ቪቫ (VIVA JANHOY! …viva mengistu!..)ብለን እንገባ ነበር፡፡ያኔም ድንገት ካየናቸው ደስታችን ወሰን የለውም ነበር፡፡የልጅ ነገር!ልጅ ሳለሁ እንደ ልጅ እጫወት ነበር …ያለው ማነው? ታዲያ ፍርሃት የተጋባበት መሌም ናዝሬት መጣ ከተባለ ከተማው በፌደራል ይወረራል፡፡ከዚያ የት እንዳደረ ሳይታወቅ ወይ ምሽቱን ሄዷል ወይ …አድሯል፡፡ካደረ ጎብዟል፡፡ግን መሌ ሶደሬ ሄዶ ያውቃል?….ቢዚ ስለነበር ምስኪን፣…. ግን ግን-ሶስቱም መሪዎችሽ ለምንፈሩሽ- ---እውነት ግን አዳማ/ናዝሬትን ለምን ፈሯት…? እስቲ እኔ ልገምት፡፡ ጊዜው በጣም ሩቅ ነው ይባላል፡፡ዓጼ ገላውዴዎስ ከግራኝ ጋር ጦርነት ገጥመዋል፡፡ጦርነቱ ተፋፍሞ ዓጼው ብዙ ከገፉ በኋላ ግራኝ ጦሩን አስተባብሮ እየገፋ ይመጣል፡፡ይሄኔ ላለመማረክ ሲዋጉ የነበሩት ንጉስ በስተመጨረሻ ይቆስላሉ በኋላም አሁን ካለው ከዓጼ ገላውዴዎስ ከፍ ብሎ ካለው ከአለሌ ወንዝ ማዶ ባለ ቦታ ተገድለው ተገኙ፡፡በኋላም ግራኝ አንገታቸውን ቆርጦ ወደ ሃረር ወስዶ በግንቡ ላ ሰቀለው የሚል ዲስኩር በገላውዴዎስ ት/ቤት ግቢ ውስጥ በ 50ኛ

2013 Human Rights Reports: Ethiopia

U.S. Department of State – 2013 Human Rights Reports: Ethiopia From the source: http://www.ethiotube.net/play/u-s-department-of-state-2013-human-rights-reports-ethiopia/ Added by webteam on February 28, 2014 in Share BUREAU OF DEMOCRACY, HUMAN RIGHTS, AND LABOR 2013 Country Reports on Human Rights Practices Report February 27, 2014 EXECUTIVE SUMMARY Ethiopia is a federal republic. The ruling Ethiopian Peoples’ Revolutionary Democratic Front (EPRDF), a coalition of four ethnically based parties, controls the government. In September 2012, following the death of former Prime Minister Meles Zenawi, parliament elected Hailemariam Desalegn as prime minister. In national parliamentary elections in 2010, the EPRDF and affiliated parties won 545 of 547 seats to remain in power for a fourth consecutive five-year term. Although the relatively few international off