Skip to main content

'My nationality'



™û|Âá¿­Œ{...............( ፪ )



አደባባይ ቆሜ አላፊ አግዳሚ ሳይ
ወሬ ጠኔ ይዞኝ ሟች ባገኝ ወይ ገዳይ፣
ወገን ባህር ማዶ ሲሰቃይ ‘ሰማለሁ
እዚህ ለሆድ ቁርጠት፣ሲባትል አያለሁ
ጉሮሮዬን ትቼ እኔ አገር እጠርጋለሁ
የት እንዳለሁ ማወቅ ማመን ፈልጌያለሁ
እህህ እሚል ባገኝ ለምን ልል ዝያለሁ
ኮምቡጦር ስር ሆኜ በ፣ በ፣ በ …እጎለጉላለሁ፤፤
ወገኔን ታዘብኩት ላሯሯጠው ሲሮጥ
አቅሉን እንደሳተ ህሊናው ሲናወጥ
ሁሉን ሆዱ እስኪፈጅ ሁሉንም ተውኩለት፤
ይልቅ ጨከንኩና…
ወሬ መፍጠር ባይችል እኔ ልፈጥርለት
እሱ የራቀውን ኮረንቲ ያዝኩለት
ራሴን በራሴ በእሳት ለኮስኩለት
ለካስ በርዶት ኖሮ ተሰብስቦ ሞቆኝ
ወሬዬን ኮምኩሞ እሳቴን አዳፍኖ፣ከነመፈጠሬ-ከነሞቴም ረሳኝ
ኢትዮጵያዊነቴ፣ የዚያን ጊዜ ገባኝ
ከዚያች ቀን ጀምሮ ዜግነትም የለኝ
ማነው ምፀተኛ የኔ ሰው የሚለኝ
በሞቴ ሞቼለት በቁም ያልገደለኝ፡፡


(ለሰማዕቱ መምህር የኔሰው ገብሬ እና በሳዑዲ ፖሊሶች ለተገደሉ ሃበሾች፡፡)

©ተስፋዬ ዋ.2006 ዓ/ም                   
ethopianwoo.blogspot.com

Comments

Popular posts from this blog

የወሲብ ግፍና ዘመን

(This post had been on my other blog since April 04,2013. Please consider the original post date while reading.) ዘመነ ወሲብ ዛሬ ዛሬ መቼም ትዳር የሚባለው ጎጆ የጋብቻ   ምሰጢር ያለበት አልመስል ብሏል፡፡ በአፀያፊ መልኩ ዎንዶችና ሴቶች ገና ጨቅላ በሚባል የጉልምስና (በዘመንኛው ቃል የፍንዳታ እድሜ ይሉታል፡፡) እድሜያቸው ወሲብ መጀመራቸውና በአስራዎቹ አጋማሽ ላይ ሲደርሱ ዓለም ሰየጠንሁ  ያለበትን የወሲብ ክህሎት ጣራ ነክተው ከዚያ ሲዳክሩ ይከረሙና በወላጅ ይሁን በኑሮ ግፊት ትዳር ይመሰርታሉ፡፡ የዚህ አዲስ አይነት ጎጆ አባላት ደግሞ በአብዛኛው የሚያስቁ ጥነዶች የሆናሉ፡፡ እነዲህ ያለው ትዳር የተመሰረተው ለገንዘብ ወይም ለውጭ ሀገር ዕድል ከሆነ፤ ተጋቢዎቹም ሆነ ገገባው ሩቅ ሳይሄድ ህጋዊ ፍች እንደሚፈፀምበት ገና የሰርጉ እለት ያውቁታል፡፡ በቤተሰብ ግፊትና በአብሮ አበዶች ሆይሆይታ የሚቀለስም ተመሳሳይ ጎጆ አለ፡፡ ብቻ ይህኛውም መቼ  እነደሚሆን አይታወቅም እንጂ ላይዘልቅ እንደሚችል ተጋቢዎቹም ሆኑ እኛ ስለጋብቻው አሁን የሰማን ሰዎች ከልምዳችን በመነሳት እርግጠኞች መሆን ንችላለን፡፡ የሆኖሆኖ የዛሬ ትዳር ምነም እክሎችን የያዘ እነደሆነ ላሰታውሳችሁ፡፡ ውሽምና ድጋፍ ባያገኝም አስከዚህኛው ትውልድ በመዝለቁ፤ ወደሽርሙጥና  እና  የዳማ በሚል ስያሜ በቡድን ለሚፈፀም ሰው ሰራሽ አረመኔያዊ ወሲብነት አድጓ፡፡ ጥነዶች በአንድ ጣራ ስር ሆነው እንኳ በተመሳሳይ ሰዓት ከተለያዩ ሰዎች ጋር በስልክ ወሲብ ራሳቸውን ያረካሉ፡፡ የነውሩ ዘመን   በአባቶቻችንና ከዚያ ቀደም ባለው ትውልድ ወሲብ በይፋ በየመንገዱ እንደልብ የሚወሳ ሳይሆን እንደነውር ...

Hino da Etiópia (voz) Ethiopia National Anthem (vocal) (source: http://s.ytimg.com)

የሷ ሱስ

የወደዷትን ልጅ እያወዳደሱ እያሞጋገሱ እንዲህ እያስደነሱ፤ ልፍታ ልተው ቢሏት እንኳንስ ፍቅሯና አይለቅህም ሱሱ! tsenawoo