Skip to main content

እሳት ወይ አበባ (ጸጋዬ ገብረ መድኅን)


ወንድ ብቻዉን ነዉ እሚያለቅስ
ከወዳጅ ከዘመድ ርቆ
አንጀቱን በአንጀቱ ታጥቆ
ተሸሽጎ ተገልሎ ተሸማቆ ተሸምቆ
ከቤተ ሰዉ ተደብቆ
መሽቶ የማታ ማታ ነዉ ሌት ነዉ የወንድ ልጅ እንባዉ
ብቻዉን ነዉ የሚፈታዉ፡፡ . . .
ብቻዉን ነዉ የሚረታዉ፡፡. . . .
ችሎ ዉጦ ተጨብጦ ተማምጦ ተጣጥሮ
በሲቃ ግት ተወጥሮ
እንደደመና ተቋጥሮ
እዉስጥ አንጀቱ ተቀብሮ . . . .
መሽቶ፣ ረፍዶ፣ ጀምበር ጠልቆ
የጨለማ ድባብ ወድቆ
በእንቅልፍ ጥላ ሲከበብ፣ በዝምታ ሲዋጥ አገር
ፍጡር ሁሉ ተስለምልሞ፣ ብቸኝነት ብቻ ሲቀር. . . .
የኋላ ኋላ ማታ
ምድር አገሩ በእፎይታ
ዓይኑን በእንቅልፍ ሲያስፈታ
ሁሉ በእረፍት ዓለምርቆ ብቸኝነት ብቻ ሲቀርብ
ያኔ ነዉ ወንድ ዓይኑ የሚረጥብ
የብቻ እንባ ወዙ እሚነጥብ፡፡

ብቻዉን ነዉ ብቻዉን ነዉ. . . .
የእንባ ጨለማ ለብሶ ነዉ
ወንድ ልጅ ወዙ እሚነጥበዉ፡፡

ዕጣዉን ብቻዉን ቆርሶ
ብቻዉን ሰቀቀን ጎርሶ
ብቻዉን ጭለማ ለብሶ
ገበናዉን ሳግ ሸፍኖ
ክብሩን በሰቆቃ አፍኖ
ሌሊት የማታ ማታ ነዉ
ሕቅ እንቁን እሚነጥበዉ
ኤሎሄዉን እሚረግፈዉ. . . .
ከዓይኑ ብሌን ጣር ተመጦ
ከአንጀቱ ሲቃ ተቆርጦ
ደም አልሞ ፍም አምጦ
ከአጽመ-ወዙ እቶን ተፈልጦ
እንደጠፈር-ብራቅ እምብርት
እንደእሳተ ገሞራ ግት
‘ርቅ ነዉ ወንድ ልጅ እንባዉ
ደም ነዉ ፍም ነዉ እሚያነነባዉ
ንጥረ ሕዋስ ነዉ ሰቆቃዉ
ረቂቅ ነዉ ምስጢር ነዉ ጣሩ . . .ብቻዉን ነዉ የሚፈታዉ
ብቻዉን ነዉ የሚረታዉ፡፡

ችሎ ዉጦ ተጨብጦ ሰቀቀኑን በሆዱ አጥሮ
በአንጀቱ ገበና ቀብሮ
ዉሎ ጭጭ እፍን ብሎ እንደደመና ተቋጥሮ
ጣሩን ዉጦ ተጣጥሮ
በሲቃ ግት ተሰትሮ. . . .
ከወዳጅ ከዘመድ ርቆ
ከቤተ-ሰዉ ተደብቆ
አንጀቱን በአንጀቱ ታጥቆ
ተሸሽጎ ተከናንቦ ተሸማቆ ተሸማቆ. . . .
የብቻ ብቸኝነቱ የጭለማ ልብሱ እስኪደርስ
በዓይን አዋጅ ሃሞቱ እንዳይረክስ
ቅስሙ በገበያ እንዳይፈስ
ተገልሎ በእኩለ-ሌት ወንድ ብቻዉን ነዉ እሚያለቅስ፡፡
Source:- የግጥም ምሽት በፌስቡክ https://www.facebook.com/groups/189373957880006/

Comments

Popular posts from this blog

የወሲብ ግፍና ዘመን

(This post had been on my other blog since April 04,2013. Please consider the original post date while reading.) ዘመነ ወሲብ ዛሬ ዛሬ መቼም ትዳር የሚባለው ጎጆ የጋብቻ   ምሰጢር ያለበት አልመስል ብሏል፡፡ በአፀያፊ መልኩ ዎንዶችና ሴቶች ገና ጨቅላ በሚባል የጉልምስና (በዘመንኛው ቃል የፍንዳታ እድሜ ይሉታል፡፡) እድሜያቸው ወሲብ መጀመራቸውና በአስራዎቹ አጋማሽ ላይ ሲደርሱ ዓለም ሰየጠንሁ  ያለበትን የወሲብ ክህሎት ጣራ ነክተው ከዚያ ሲዳክሩ ይከረሙና በወላጅ ይሁን በኑሮ ግፊት ትዳር ይመሰርታሉ፡፡ የዚህ አዲስ አይነት ጎጆ አባላት ደግሞ በአብዛኛው የሚያስቁ ጥነዶች የሆናሉ፡፡ እነዲህ ያለው ትዳር የተመሰረተው ለገንዘብ ወይም ለውጭ ሀገር ዕድል ከሆነ፤ ተጋቢዎቹም ሆነ ገገባው ሩቅ ሳይሄድ ህጋዊ ፍች እንደሚፈፀምበት ገና የሰርጉ እለት ያውቁታል፡፡ በቤተሰብ ግፊትና በአብሮ አበዶች ሆይሆይታ የሚቀለስም ተመሳሳይ ጎጆ አለ፡፡ ብቻ ይህኛውም መቼ  እነደሚሆን አይታወቅም እንጂ ላይዘልቅ እንደሚችል ተጋቢዎቹም ሆኑ እኛ ስለጋብቻው አሁን የሰማን ሰዎች ከልምዳችን በመነሳት እርግጠኞች መሆን ንችላለን፡፡ የሆኖሆኖ የዛሬ ትዳር ምነም እክሎችን የያዘ እነደሆነ ላሰታውሳችሁ፡፡ ውሽምና ድጋፍ ባያገኝም አስከዚህኛው ትውልድ በመዝለቁ፤ ወደሽርሙጥና  እና  የዳማ በሚል ስያሜ በቡድን ለሚፈፀም ሰው ሰራሽ አረመኔያዊ ወሲብነት አድጓ፡፡ ጥነዶች በአንድ ጣራ ስር ሆነው እንኳ በተመሳሳይ ሰዓት ከተለያዩ ሰዎች ጋር በስልክ ወሲብ ራሳቸውን ያረካሉ፡፡ የነውሩ ዘመን   በአባቶቻችንና ከዚያ ቀደም ባለው ትውልድ ወሲብ በይፋ በየመንገዱ እንደልብ የሚወሳ ሳይሆን እንደነውር ...

እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ

እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ የዓለም ሊቀ ሊቃውንት፣ የኪነ ጥበብ ምሑር የተከበሩ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ (ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም- ሚያዝያ ፪ ቀን ፳፻፬ ዓ/ም)፤ ‘’ኪነ ጥበብ የሰው ልጅን መንፈስ ለማዳበር፣ ሀገራችንን ለማሳደግ፣ ለማሳወቅ እና ለሕይወታዊ ኑሮ ተስፋ ለመፍጠር የላቀ ሚና ይጫወታል’’ ይላሉ። ለጥቀውም ‘’ዛሬ የምንሠራው ሥራ የዛሬን ሕይወት እያንጸባረቀ ለነገው ትውልድ ፈር መቅደድ አለበት፡፡” በሚል ስሜት ኪን ማንኛውንም የሰው ኑሮ ረገድ የሚነካ እንደሆነ ያስረግጣሉ። በዓለም የታወቁና የተከበሩት ኢትዮጵያዊ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በሰሜን ሸዋ በምትገኘው የሸዋ ነገሥታት ከተማ አንኮበር ላይ ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም ከአባታቸው አቶ ተክሌ ማሞ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ፈለቀች የማታወርቅ ተወለዱ። ገና በጨቅላ ዕድሜያቸው ፋሺስት ኢጣልያ ኢትዮጵያን በግፍ ሲወራት፣ የልጅነት ትዝታቸውም ይሄው የግፍ ወረራ እና ጦርነት የሚያስከትለው የሰው፣ የንብረት እና የባህል ጥፋት ፤ ከነጻነትም በኋላ ዐቢዩ ሥራ በወረራ የተበላሸችውን ሀገራቸውን እንደገና መገንባት እንደሆነ ነው። ለዚህም የሀገር ግንባታ አስፈላጊውን እውቀት መሸመት የፈለጉት በ ማዕድን ምሕንድስና ዘርፍ ነበር። ወላጆቻቸውና ዘመድ አዝማዶች ግን የኪነ ጥበብ ስጦታቸውን በቤታቸውና በከተማው ዙሪያ በሚስሏቸው ስዕሎች ተገንዝበውት ነበር። የመጀመሪያና መካከለኛ ትምህርታቸውን የት እና መቼ እንዳጠናቀቁ የተጻፈ መረጃ ባናገኝም፤ ገና በአሥራ አምስት ዓመታቸው በ ፲፱፻፵ ዓ/ም ለከፍተኛ ትምህርት ተመርጠው የምሕንድስና ትምህርታቸውን ለመከታተል ወደ እንግሊዝ አገር ይላካሉ። ተሰዳጅ ተማሪ ወጣቶቹ ንጉሠ ነገሥቱን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ሲሰናበቱ፣ አፈወርቅ ተክሌ ጃንሆይ የ...

ይብላኝ…

ችግር ወላፈኑ ጠብሶሽ በላብሽ ፍሳሽ ልታብሽው እንደዋዛ ካገር ወተሽ ደፋ ብለሽ ለቀረሽው በደሌን አሁን አወኩት ምትክ በሌለው ብዕርሽ ሰቆቃሽ ገፍቶ በፃፍሽው በድንጋይ ላይ ትርክትሽ በሞትሽ ቃል ገለፅሽው እህቴ ልናዘዝ ስሚኝ በባዕድ ሀገር ወርውሬ የገደልኩሽ እኔነኝ ስሚኝ… የጅብ ከሄደ ጩኸቴን የምፀት ቃል ምሬቴን የፍርሀት ጠርዝ መልክቴን የምላስ ተርፍ በረከቴን ይብላኝ… ያያትሽን ግብር ሳልፈፅም በሞቴ ሂወት ሳልሰጥሽ ከጠላትሽ ጋር አብሬ እኔው በጅ አዙር ገደልኩሽ ይብላኝ… የሞትሽ ፀፀት ሳይበቃኝ እንደገና ልገልሽ በሰልፍ ወደሞት ስቴጂ ዝም ብዬ ለማይሽ ይብላኝ… የሰው ትርፍ አርጌ እንደ አይረባ ለጣልኩት ውርደትሽን ክብር አርጌ በደምሽ ወዝ ለራስኩት የናቴ ልጅ… እኔን ይድፋኝ ልበልሽ ልደፋ ይድረሰኝ ፅዋሽ ነፃ ማውጣቱ ቢያቅተኝ ሞትሽን ባፌ ልጋራሽ /ፀደቀ ድጋፌ/