Skip to main content

ፖለቲኳስ ቢሆን...!



                                                                                                                                      19/10/2006
ኳስ ክብ መሆኗ ብቻ ለአለም መነጋገሪያ አላደረጋትም፡፡ በእግር መለወሷም ከቶ አላስናቃትም፡፡ ብዙ ሚሊዮኖችን ታስፈነጥዛለች፤ ብዙ ሚሊዮኖችን ታስመነዝራለች፤ ለብዙ ሚሊዮኖች የስራ እድል ፈጥራ እንጀራ ታበላለች፡፡ ሊያውም “fair play” የሚል የሚዛንን አድልዎ የሚኮንን መፈክር አንግባ! ይልቁንም አለሙን ሁሉ በአንድ ቋንቋ ታዘምራለች፡፡
የግል ብቃትና ልዩ ክህሎት፣የቡድን ስራ እና ቁርጠኛ አመራር፣ የላቀ አፈፃፀም ያለውን ጠንካራ ቡድን ይመሰርታሉ፡፡ ምግብ፣ አልባስ፣ እና መጠለያ፤ የጤና ባለሙያ፣ የስነልቦና አማካሪ፣ ወኔ ወስቃሽ እና ሌሎች ሁሉ ስለ ቡድኑ ውጤት የበኩላቸውን አስተዋፅዖ እረገው በሚመዘገበው ድል ይረካሉ፣ ይቦርቃሉ፡፡ እንኳንና እነሱ ደጋፊዎች በሩቅ ሆነው እርሳቸውን እስኪስቱ  ይደሰታሉ፤ ስለ ድሉ ይዘምራሉ፤ በየቅፅበቱ በሚፈጠሩ ሁኔታዎች ሁሉ በጉጉት ይወራጫሉ፤ በቁጭት ይንገበገባሉ፡፡
ይህ ሁሉ የሚሆነው ግን  ኳስ ገደብ ስላላት፣ እንዲሁም የተጫዋች ቅያሬ ልክ፤ የመለዮ ልብስ አግባብ፤ የግብ ሁኔታ፤ የመከላከልና የአፀፋ ምላሽ፤ ዝላይ፣ መንሸራተት፣ የእጅ ጣልቃ ገብነት፤ የማንቂያ ደውል(ፊሽካ፤) … ብቻ ሁሉም ገደብ አለው፡፡
እነዚህ ገደቦቸች ቢጣሱ የሚያስከትሉት ቅጣት አለ፡፡ ገደቦቹም ሆነ ቅጣቶቹ ለሕዝብ በማያሻማ መልኩ ይቀመጣሉ፡፡ በየደረጃውም በሰፈር ጨዋታዎች ሳይቀሩ ይተገበራሉየበላይ   ጠባቂም አላቸው፡፡ እነርሱም የሚየሻሙ ነጥቦችን ከዘመኑ ጋር እየዘመነ በሚሄደው ቴክኖሎጂ ሳይቀር እየታገዙ የጨዋታውን ተወዳጅነት በ“fair play” መፈክርነት ለማስቀጠል ይተጉለታል፡፡
የኳስ ሜዳ ነገር እንኳንስ እለት እለት ትኩረት ሰጥቶት ቤተሰብ ለሆነው ይቅርና እንደኛ ባጋጣሚ እግር ሲጥለው ለሚያየው እንኳ በፍቅር ትንፋሽን የሚያስውጥ ወደረኛ መስክ ነው፡፡ እነዲያውም ሀገርን የመነግዛት የፖለቲካ ጨዋታ በኳስ ሜዳ ህግ ቢመራ አያሰኝምና ነው?!
በተንኮል መሰንዘርና ማጥቃት ቢጫ/ቀይ እና የቅጣት ምት ቢያሰስከትሉ፤ ከሚገባው በላይ ሹም ሽረት ለማድረግ አሰልጣኙ ገደብ ቢኖርበት፤ ከመስመር ውጭ በወጣ ኳስ ራስን ለመከላከልም ሆነ ተቀናቃኝን ለማጥቃት እንዳይቻል የመስመር ዳኛው እንደሚጠባበቅ በስልጣን ላይ ያለው ፖለቲከኛ ሀይ ባይ ቢኖረው፤ እንደ “Goal-line” ቴክኖሎጂ የምርጫ ኮሮጆ ላይ እፍረት እንዳይኖር ውጤት መጠበቂያ ቢበጅለት፤ በጉጉት የማጥቃት ውጤት ላይ ላሉት ከጨዋታ ውጪ(off side) ምልክት ቢውለበለብ፤
ጉዳት የደረሰበት ወይም የተበደለ እጁን ከፍ አድርጎ ምልክት የሚሰጠውና አይቶ የሚቨይንለት ጤናማ ዳኛ ቢሰየም፤ በዕድ አካላትን ወይም ተደራቢ የመጫወቻ ኳስን አለያም ህገ-ተላላፊ አሰልጣኝን ከሜዳ የማስወጣት መብት ያለው ዳኛ ቢቆም፤ በትክክል ግብ ላገባው ወይም ለግቡ አስተዋጥዖ የሆነውን ሰው እና እንቅስቃሴ ተመልካች በማያሻማ መልኩ የሚያስችል ማሳያ(Re-play) ቢኖር፤
ቢጫና ቀይ ካርድ አይተው ከሜዳ የተወገዱ ተጫዋቾች ቅጣታቸውን ጨርሰው እነደሚመለሱት በፖለቲካ የቆሰሉና የታሰሩት በግልፅ ህግ ከሆነ ከቅጣት መልስ ቢሰለፉ፤ በጉዳት  ከሜዳ ውጭ ስለሆኑ ተጫዋቾች ሳይወሸከት  ለህዝብ ይፋ ቢሆን፤ … ወዘተ፡፡
አዎ! በበርካቶች ዘንድ ተወዳጅነት ያለው እግር ኳስ ዛሬም በብራዚል የአለም ዋንጫ ፉክክር የሚዮኖችን ልብ እንደሰቀለ ቀጥሏል፡፡ ኳስ ክብ ናትና ነገ ደግሞ በሌላ ስፍራ እንጠብቃታለን፡፡ ይህ ሁሉ የሚሆነው በዘጠና ደቂቃ የጊዜ ገደብ የታጠረች በመሆኗ ነው፡፡ የባከነ ሰዓት በአግባብ ይካሳል፡፡ በአንዳች ያለገደብ መንዛዛት የለም፡፡ ይህ የዘጠና ደቂቃ ገደብ ባይኖር  ተጨዋቾች ይደክማሉ፣ ተቀናቃኛቸውን ሮጠው ኳስ ማስጣል ሰረለማይቻላቸው ትግል፣ ግፊያና ጠረባ ያበዛሉ፤ በሜዳ ተዝለፍልፈው የሚወድቁም፣ በዚያው ያሸለቡም አሉ፡፡ ስለዚህ የጊዜ ገደብ መኖሩ የግድ ጠቃሚ ይሆናል፡፡
የኛ ሀገር ስልጣን ግን ገና ብዙ ያልተቀመጡለትና የማይከበሩ ህጎችና ገደቦች አሉት፡፡ ስልጣን ስራ ሳይሆን ትዳር የሆነባቸው አቅም አጥተው ተዝለፍልፈው ስላልወደቁ ብቻ ሰማኒያ እንደመቅደድ አሳፍሯቸው የሙጥኝ ብለውት እየተዝለፈለፉ አንዳንዶችም ጭራሽ በስልጣን ሜዳ ወድቀው ሲሞቱ እያየን ነው፡፡
ዋይ! አለማዊም፤ አፍሪካዊም፤ ኢትዮጲያዊም ባልሆን ፖለቲኳስ እንደግርኳስ በ“fair play” ብትመራ ደስ ይለኝና በነገር ሁሉ መከፋቴ ይቀርልኝ አልነበረምና ነው?!

Comments

Popular posts from this blog

Hino da Etiópia (voz) Ethiopia National Anthem (vocal) (source: http://s.ytimg.com)

The man who taught Mandela to be a soldier

       The man who taught Mandela to be a soldier By Penny Dale BBC Africa, Addis Ababa In July 1962, Col Fekadu Wakene taught South African political activist Nelson Mandela the tricks of guerrilla warfare - including how to plant explosives before slipping quietly away into the night. Mr Mandela was in Ethiopia, learning how to be the commander-in-chief of Umkhonto we Sizwe - the armed wing of the African National Congress (ANC). The group had announced its arrival at the end of 1961 by blowing-up electricity pylons in various places in South Africa. Then on 11 January 1962, Mr Mandela had secretly, and illegally, slipped out of South Africa. His mission was to meet as many African political leaders as possible and garner assistance for the ANC, including money and training for its military wing. And to be moulded into a soldier himself. During this trip, he visited Ethiopia twice and left a deep impression on those who met ...

እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ

እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ የዓለም ሊቀ ሊቃውንት፣ የኪነ ጥበብ ምሑር የተከበሩ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ (ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም- ሚያዝያ ፪ ቀን ፳፻፬ ዓ/ም)፤ ‘’ኪነ ጥበብ የሰው ልጅን መንፈስ ለማዳበር፣ ሀገራችንን ለማሳደግ፣ ለማሳወቅ እና ለሕይወታዊ ኑሮ ተስፋ ለመፍጠር የላቀ ሚና ይጫወታል’’ ይላሉ። ለጥቀውም ‘’ዛሬ የምንሠራው ሥራ የዛሬን ሕይወት እያንጸባረቀ ለነገው ትውልድ ፈር መቅደድ አለበት፡፡” በሚል ስሜት ኪን ማንኛውንም የሰው ኑሮ ረገድ የሚነካ እንደሆነ ያስረግጣሉ። በዓለም የታወቁና የተከበሩት ኢትዮጵያዊ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በሰሜን ሸዋ በምትገኘው የሸዋ ነገሥታት ከተማ አንኮበር ላይ ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም ከአባታቸው አቶ ተክሌ ማሞ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ፈለቀች የማታወርቅ ተወለዱ። ገና በጨቅላ ዕድሜያቸው ፋሺስት ኢጣልያ ኢትዮጵያን በግፍ ሲወራት፣ የልጅነት ትዝታቸውም ይሄው የግፍ ወረራ እና ጦርነት የሚያስከትለው የሰው፣ የንብረት እና የባህል ጥፋት ፤ ከነጻነትም በኋላ ዐቢዩ ሥራ በወረራ የተበላሸችውን ሀገራቸውን እንደገና መገንባት እንደሆነ ነው። ለዚህም የሀገር ግንባታ አስፈላጊውን እውቀት መሸመት የፈለጉት በ ማዕድን ምሕንድስና ዘርፍ ነበር። ወላጆቻቸውና ዘመድ አዝማዶች ግን የኪነ ጥበብ ስጦታቸውን በቤታቸውና በከተማው ዙሪያ በሚስሏቸው ስዕሎች ተገንዝበውት ነበር። የመጀመሪያና መካከለኛ ትምህርታቸውን የት እና መቼ እንዳጠናቀቁ የተጻፈ መረጃ ባናገኝም፤ ገና በአሥራ አምስት ዓመታቸው በ ፲፱፻፵ ዓ/ም ለከፍተኛ ትምህርት ተመርጠው የምሕንድስና ትምህርታቸውን ለመከታተል ወደ እንግሊዝ አገር ይላካሉ። ተሰዳጅ ተማሪ ወጣቶቹ ንጉሠ ነገሥቱን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ሲሰናበቱ፣ አፈወርቅ ተክሌ ጃንሆይ የ...