ሞቱን የገደለ አንድ ሰው ተገኘ
ጭቆናን ረግጦ በልዕልና የናኘ
ሲታሰር
ያስፈታ ሲለቀቅ የፈታ
ሲሞት ያልገደለ ሲነሳ ይበረታ!
ይልክልን ይሆን መንፈሱን መፅናኛ
እምነቱን ፅናቱን ትዕግስቱን ስለእኛ
አይጠረጠርም-ዛሬም ትላንትና
መንፈሱ አብሮን አለ ሲያጀግን- ሲያፅናና
የሮቢን ባህታዊ -
እነሱ እነደሚሉን- የጥቁር ሰብዓዊ
አካልን መንፈስን በአንድ አስተባብሮ
ነፃነት ያወጀ በህገ-ተፈጥሮ
ከኢየሱስ ቀጥሎ ሚስጥር የነገረን
እውነትን በተግባር ቀምሶ ያስተማረን
ማንዴላ ሕያው ነው በመኖሩ ያኖረን
ሲሞት
ያልገደለን፡፡
ተስፋዬ
ዋቅቶላ 27/03/2006 ዓ/ም ናዝሬት-ኢትዮጵያ
Comments
Post a Comment