Skip to main content

ፖለቲኳስ ቢሆን...!



                                                                                                                                      19/10/2006
ኳስ ክብ መሆኗ ብቻ ለአለም መነጋገሪያ አላደረጋትም፡፡ በእግር መለወሷም ከቶ አላስናቃትም፡፡ ብዙ ሚሊዮኖችን ታስፈነጥዛለች፤ ብዙ ሚሊዮኖችን ታስመነዝራለች፤ ለብዙ ሚሊዮኖች የስራ እድል ፈጥራ እንጀራ ታበላለች፡፡ ሊያውም “fair play” የሚል የሚዛንን አድልዎ የሚኮንን መፈክር አንግባ! ይልቁንም አለሙን ሁሉ በአንድ ቋንቋ ታዘምራለች፡፡
የግል ብቃትና ልዩ ክህሎት፣የቡድን ስራ እና ቁርጠኛ አመራር፣ የላቀ አፈፃፀም ያለውን ጠንካራ ቡድን ይመሰርታሉ፡፡ ምግብ፣ አልባስ፣ እና መጠለያ፤ የጤና ባለሙያ፣ የስነልቦና አማካሪ፣ ወኔ ወስቃሽ እና ሌሎች ሁሉ ስለ ቡድኑ ውጤት የበኩላቸውን አስተዋፅዖ እረገው በሚመዘገበው ድል ይረካሉ፣ ይቦርቃሉ፡፡ እንኳንና እነሱ ደጋፊዎች በሩቅ ሆነው እርሳቸውን እስኪስቱ  ይደሰታሉ፤ ስለ ድሉ ይዘምራሉ፤ በየቅፅበቱ በሚፈጠሩ ሁኔታዎች ሁሉ በጉጉት ይወራጫሉ፤ በቁጭት ይንገበገባሉ፡፡
ይህ ሁሉ የሚሆነው ግን  ኳስ ገደብ ስላላት፣ እንዲሁም የተጫዋች ቅያሬ ልክ፤ የመለዮ ልብስ አግባብ፤ የግብ ሁኔታ፤ የመከላከልና የአፀፋ ምላሽ፤ ዝላይ፣ መንሸራተት፣ የእጅ ጣልቃ ገብነት፤ የማንቂያ ደውል(ፊሽካ፤) … ብቻ ሁሉም ገደብ አለው፡፡
እነዚህ ገደቦቸች ቢጣሱ የሚያስከትሉት ቅጣት አለ፡፡ ገደቦቹም ሆነ ቅጣቶቹ ለሕዝብ በማያሻማ መልኩ ይቀመጣሉ፡፡ በየደረጃውም በሰፈር ጨዋታዎች ሳይቀሩ ይተገበራሉየበላይ   ጠባቂም አላቸው፡፡ እነርሱም የሚየሻሙ ነጥቦችን ከዘመኑ ጋር እየዘመነ በሚሄደው ቴክኖሎጂ ሳይቀር እየታገዙ የጨዋታውን ተወዳጅነት በ“fair play” መፈክርነት ለማስቀጠል ይተጉለታል፡፡
የኳስ ሜዳ ነገር እንኳንስ እለት እለት ትኩረት ሰጥቶት ቤተሰብ ለሆነው ይቅርና እንደኛ ባጋጣሚ እግር ሲጥለው ለሚያየው እንኳ በፍቅር ትንፋሽን የሚያስውጥ ወደረኛ መስክ ነው፡፡ እነዲያውም ሀገርን የመነግዛት የፖለቲካ ጨዋታ በኳስ ሜዳ ህግ ቢመራ አያሰኝምና ነው?!
በተንኮል መሰንዘርና ማጥቃት ቢጫ/ቀይ እና የቅጣት ምት ቢያሰስከትሉ፤ ከሚገባው በላይ ሹም ሽረት ለማድረግ አሰልጣኙ ገደብ ቢኖርበት፤ ከመስመር ውጭ በወጣ ኳስ ራስን ለመከላከልም ሆነ ተቀናቃኝን ለማጥቃት እንዳይቻል የመስመር ዳኛው እንደሚጠባበቅ በስልጣን ላይ ያለው ፖለቲከኛ ሀይ ባይ ቢኖረው፤ እንደ “Goal-line” ቴክኖሎጂ የምርጫ ኮሮጆ ላይ እፍረት እንዳይኖር ውጤት መጠበቂያ ቢበጅለት፤ በጉጉት የማጥቃት ውጤት ላይ ላሉት ከጨዋታ ውጪ(off side) ምልክት ቢውለበለብ፤
ጉዳት የደረሰበት ወይም የተበደለ እጁን ከፍ አድርጎ ምልክት የሚሰጠውና አይቶ የሚቨይንለት ጤናማ ዳኛ ቢሰየም፤ በዕድ አካላትን ወይም ተደራቢ የመጫወቻ ኳስን አለያም ህገ-ተላላፊ አሰልጣኝን ከሜዳ የማስወጣት መብት ያለው ዳኛ ቢቆም፤ በትክክል ግብ ላገባው ወይም ለግቡ አስተዋጥዖ የሆነውን ሰው እና እንቅስቃሴ ተመልካች በማያሻማ መልኩ የሚያስችል ማሳያ(Re-play) ቢኖር፤
ቢጫና ቀይ ካርድ አይተው ከሜዳ የተወገዱ ተጫዋቾች ቅጣታቸውን ጨርሰው እነደሚመለሱት በፖለቲካ የቆሰሉና የታሰሩት በግልፅ ህግ ከሆነ ከቅጣት መልስ ቢሰለፉ፤ በጉዳት  ከሜዳ ውጭ ስለሆኑ ተጫዋቾች ሳይወሸከት  ለህዝብ ይፋ ቢሆን፤ … ወዘተ፡፡
አዎ! በበርካቶች ዘንድ ተወዳጅነት ያለው እግር ኳስ ዛሬም በብራዚል የአለም ዋንጫ ፉክክር የሚዮኖችን ልብ እንደሰቀለ ቀጥሏል፡፡ ኳስ ክብ ናትና ነገ ደግሞ በሌላ ስፍራ እንጠብቃታለን፡፡ ይህ ሁሉ የሚሆነው በዘጠና ደቂቃ የጊዜ ገደብ የታጠረች በመሆኗ ነው፡፡ የባከነ ሰዓት በአግባብ ይካሳል፡፡ በአንዳች ያለገደብ መንዛዛት የለም፡፡ ይህ የዘጠና ደቂቃ ገደብ ባይኖር  ተጨዋቾች ይደክማሉ፣ ተቀናቃኛቸውን ሮጠው ኳስ ማስጣል ሰረለማይቻላቸው ትግል፣ ግፊያና ጠረባ ያበዛሉ፤ በሜዳ ተዝለፍልፈው የሚወድቁም፣ በዚያው ያሸለቡም አሉ፡፡ ስለዚህ የጊዜ ገደብ መኖሩ የግድ ጠቃሚ ይሆናል፡፡
የኛ ሀገር ስልጣን ግን ገና ብዙ ያልተቀመጡለትና የማይከበሩ ህጎችና ገደቦች አሉት፡፡ ስልጣን ስራ ሳይሆን ትዳር የሆነባቸው አቅም አጥተው ተዝለፍልፈው ስላልወደቁ ብቻ ሰማኒያ እንደመቅደድ አሳፍሯቸው የሙጥኝ ብለውት እየተዝለፈለፉ አንዳንዶችም ጭራሽ በስልጣን ሜዳ ወድቀው ሲሞቱ እያየን ነው፡፡
ዋይ! አለማዊም፤ አፍሪካዊም፤ ኢትዮጲያዊም ባልሆን ፖለቲኳስ እንደግርኳስ በ“fair play” ብትመራ ደስ ይለኝና በነገር ሁሉ መከፋቴ ይቀርልኝ አልነበረምና ነው?!

Comments

Popular posts from this blog

እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ

እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ የዓለም ሊቀ ሊቃውንት፣ የኪነ ጥበብ ምሑር የተከበሩ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ (ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም- ሚያዝያ ፪ ቀን ፳፻፬ ዓ/ም)፤ ‘’ኪነ ጥበብ የሰው ልጅን መንፈስ ለማዳበር፣ ሀገራችንን ለማሳደግ፣ ለማሳወቅ እና ለሕይወታዊ ኑሮ ተስፋ ለመፍጠር የላቀ ሚና ይጫወታል’’ ይላሉ። ለጥቀውም ‘’ዛሬ የምንሠራው ሥራ የዛሬን ሕይወት እያንጸባረቀ ለነገው ትውልድ ፈር መቅደድ አለበት፡፡” በሚል ስሜት ኪን ማንኛውንም የሰው ኑሮ ረገድ የሚነካ እንደሆነ ያስረግጣሉ። በዓለም የታወቁና የተከበሩት ኢትዮጵያዊ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በሰሜን ሸዋ በምትገኘው የሸዋ ነገሥታት ከተማ አንኮበር ላይ ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም ከአባታቸው አቶ ተክሌ ማሞ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ፈለቀች የማታወርቅ ተወለዱ። ገና በጨቅላ ዕድሜያቸው ፋሺስት ኢጣልያ ኢትዮጵያን በግፍ ሲወራት፣ የልጅነት ትዝታቸውም ይሄው የግፍ ወረራ እና ጦርነት የሚያስከትለው የሰው፣ የንብረት እና የባህል ጥፋት ፤ ከነጻነትም በኋላ ዐቢዩ ሥራ በወረራ የተበላሸችውን ሀገራቸውን እንደገና መገንባት እንደሆነ ነው። ለዚህም የሀገር ግንባታ አስፈላጊውን እውቀት መሸመት የፈለጉት በ ማዕድን ምሕንድስና ዘርፍ ነበር። ወላጆቻቸውና ዘመድ አዝማዶች ግን የኪነ ጥበብ ስጦታቸውን በቤታቸውና በከተማው ዙሪያ በሚስሏቸው ስዕሎች ተገንዝበውት ነበር። የመጀመሪያና መካከለኛ ትምህርታቸውን የት እና መቼ እንዳጠናቀቁ የተጻፈ መረጃ ባናገኝም፤ ገና በአሥራ አምስት ዓመታቸው በ ፲፱፻፵ ዓ/ም ለከፍተኛ ትምህርት ተመርጠው የምሕንድስና ትምህርታቸውን ለመከታተል ወደ እንግሊዝ አገር ይላካሉ። ተሰዳጅ ተማሪ ወጣቶቹ ንጉሠ ነገሥቱን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ሲሰናበቱ፣ አፈወርቅ ተክሌ ጃንሆይ የ

I am an Oromo too! ስለምን ይዘበትብናል…?

እኛ በሰው አምሳል መፈጠራችንንና ከናንተው እኩል የሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ሰዎች ስለመሆናችን እንዴት ተዘነጋችሁ! ቀደምት አባቶቻችን ስንቶቹን ደራሽ ያጡ የሀገራችንን ኢትዮጲያ ልጆች ጡት እያጠቡ ከአብራካቸው ከወጡ ልጆቻቸው እኩል እያስተማሩና ሀብት ንብረት እያወረሱ ለወግ ማዕረግ ያበቁ መሆናቸው ተረሳችሁ…? ኢትዮጲያዊነትን ከኦሮሞ ሕዝብ፤ የኦሮሞን ህዝብ ከኢትዮጲያዊነት በመነጣጠል የምታገኙት ልዩ ጥቅም እነደሚኖር ሳይታለም የተፈታ መሆኑ በየጓዳው የሚወራው ለዚህም አይደል ብላችሁ እነዴት አልጠረጠራችሁም…? ሕዝቡ ሁሉ ተጠርጣሪ (ሊያውም በሽብርተኝነት) ተብሎ በይፋ እስር ቤት   እንዲገባ የሚቻላችሁ መስሏችሁ ይሆን…? እንኪያስ የትኛውን ሕዝብ ልትመሩት ነው…?(ይቅርታ በአይንህን ጨፍን ላሞኝህ ልትነግዱበት ነው…?- ለማለት ፈልጌ ነው፡፡) ለነገሩ ዞን 9ኞችን የመፍጠሩ ስትራቴጂ ሲነቃባችሁ ዞን 9 ነዋሪውን ትታችሁ ብሎገሮቹን ታስሩ ታንገላቱ ታሳድዱ ዘንድስ ማን አይዟችሁ እንዳላችሁ ምን ይታወቃል…? ይህች ፅሁፍ እንኳ ካቅሟ በመንግስታችሁ እውቅና አግኝታ ከመነበብና የፀሃፊውን መብት ከማስከበር ትታገድ ይሆናል፡፡ ማን ያውቃል…? ዓለም ሁሉ በንግድ /ቢዝነስ/ ፅንሰ ሃሳብ በተወጠረችበት በዚህ ዘመን የኋሊዮሽ የተንቋሸሸሽንበት ያህል እንዲሰማን የተደረግንባቸውን የሀገራችንን ታሪክ እየባዘታችሁ ስለምን የትውልዱን ተስፋ በቁንፅል ሃሳብ በመወጠር ትቀጩብናላችሁ…? እናንተ የምትገነቡትን ሕንፃ፣ ለሎችን በመጨቆን ስንጥቅ የምታተርፉበትን ንግድ፣ በሀሰት ህዝብን እየሸነገላችሁ የምትቸበችቡትን መሬት፣ የምታቀያይሯቸውን መኪኖች፣ ህዝብ የሚያውቃቸውና የማያውቃቸው በአጭር ጊዜ የምትበለፅጉባቻው መንገዶች ሁሉ ከዓይንና ከህሊናችን የተሰወሩ ይመስላችሁ ይሆን…?

Seeing the Arcs off , Nazareth main road

 Nazareth / Adama like all other cities and towns has very colorfully celebrated the Ethiopian Epiphany, `Timket` both religiously and culturally. Some funny  moments were on public by individuals and small group; including school children songs that used to be experienced in music periods or teaching help. Watch video here under.     See ...        more ...                 photo...