Skip to main content

ናዝሬትዬ መሪዎችሽ ለምን ይፈሩሻል?

https://www.facebook.com/twaktola
ናዝሬትዬ መሪዎችሽ ለምን ይፈሩሻል?
ድሮም ጃንሆይ ናዛሬት/አዳማ መምጣት አይወዱም ነበር፣ይባላል፡፡በዚህም የተነሳ ለገላውዴዎስ ት/ቤት መሰረትና ምርቃት ከመምጣታቸው ውጪ ሌላ ጊዜ መች እንደመጡ ሲነገርም አልሰማሁም፡፡መንጌም ሲመጣ በጣም ተደብቆና በድንገት ሲሆን ፣የማስታውሰው ለናዝሬት ቴክኒክ ኮሌጅ (የዛሬው አዳማ ዩኒቨርሲቲ) መሰረትና ምርቃት መምጣቱን ነው፡፡ከዚያ በተረፈ ሁለቱም መሪዎች ወደ ሶደሬ ሲያልፉ ረዥም እድሜ ተመኙ ተብሎ ሕፃናት ወጥተን ቪቫ (VIVA JANHOY! …viva mengistu!..)ብለን እንገባ ነበር፡፡ያኔም ድንገት ካየናቸው ደስታችን ወሰን የለውም ነበር፡፡የልጅ ነገር!ልጅ ሳለሁ እንደ ልጅ እጫወት ነበር …ያለው ማነው?
ታዲያ ፍርሃት የተጋባበት መሌም ናዝሬት መጣ ከተባለ ከተማው በፌደራል ይወረራል፡፡ከዚያ የት እንዳደረ ሳይታወቅ ወይ ምሽቱን ሄዷል ወይ …አድሯል፡፡ካደረ ጎብዟል፡፡ግን መሌ ሶደሬ ሄዶ ያውቃል?….ቢዚ ስለነበር ምስኪን፣….
ግን ግን-ሶስቱም መሪዎችሽ ለምንፈሩሽ- ---እውነት ግን አዳማ/ናዝሬትን ለምን ፈሯት…?
እስቲ እኔ ልገምት፡፡
ጊዜው በጣም ሩቅ ነው ይባላል፡፡ዓጼ ገላውዴዎስ ከግራኝ ጋር ጦርነት ገጥመዋል፡፡ጦርነቱ ተፋፍሞ ዓጼው ብዙ ከገፉ በኋላ ግራኝ ጦሩን አስተባብሮ እየገፋ ይመጣል፡፡ይሄኔ ላለመማረክ ሲዋጉ የነበሩት ንጉስ በስተመጨረሻ ይቆስላሉ በኋላም አሁን ካለው ከዓጼ ገላውዴዎስ ከፍ ብሎ ካለው ከአለሌ ወንዝ ማዶ ባለ ቦታ ተገድለው ተገኙ፡፡በኋላም ግራኝ አንገታቸውን ቆርጦ ወደ ሃረር ወስዶ በግንቡ ላ ሰቀለው የሚል ዲስኩር በገላውዴዎስ ት/ቤት ግቢ ውስጥ በ 50ኛ ዓመት የት/ቤቱ በዓል ላይ ከታወቁ የከተማው ያገር ሽማግሌ ሰምቻለኁ፡፡እንግዲህ የኔ ግምት ከዚህ ንግግር ጋር ይያዛል፡፡
ደም የለመደ አስፋልት ፣ደም የለመደ ሜዳ፣ደም የለመደ…እየተባለ ሲስፈራራ መቼም ሳትሰሙ አትቀሩም ፡፡ እንግዲህ የተራ ሰዎቹ ሳያሆን የታላላቅ መሪዎቻችን የአዳማ ሆነ የናዝሬት ፍርሃት ከዚህ የሚመነጭ ይመስለኛል፡፡ካልሆነ ከምን ሊሆን ይችላል;…ነው ወይስ ከጥላቻ;….በእርግጥ ናዝሬቶች በጋራ በተከበበች ከተማችን የማይበጀንን መውጫ ማሳጣቱን እናውቅበታለን፡፡ካልሆነ እርም ብሎ ይወጣታል እንጂ በቀላሉ አንለቀውም፡፡ለዚህም ይሆናል በጥቂት አመታት ውስጥ ብቻ ከ14 በላ ይ ከንቲባ ሲመጣና ሲባረር የታየባት፡፡አይመቹንም እኛም አንመቻቸውም ፡፡ታዲያ እኮ ምናለ ቢተውን !...አሊያም የራሳችንነ ከንቲባ ራሳችን እንድንመርጥ ነፃነታችንን ቢመልሱልን፡፡
በመጨረሻ አንድ ቀልድ ቢጤ ልንገራችሁ፡፡
ሙስና የማይቀበል ከንቲባ መጣላት ተባለና 6 ወር ሙሉ ተወራ፡፡ያ ሰው የ6ወር ሪፖርት በግልፅ ሊያሰማና ከህዝቡ አስተያየት ሊሰበስብ በተንጣለለው የኦሊያድ አዳራሽ ኅዝቡን ያወያያል፡፡በከተማው ስላለው ጃንሆይ ስላሰሩት ሆስፒታል እየተወራ ነው፡፡እሱ የአዳማ ሆስፒታል እያለ ያትታል፡፡ ህዝቡ ደሞ የኀይለ ማርያም ማሞ ሆ/ል እያለ ችግሩን ይገልፃል፡፡በኋላ ሰብሳቢው አዲሱ ከንቲባ ግራ እንደተጋባ በሚገልጽ ሁኔታ ሆኖ ሲቆጣ ማዳመጥ ጀመረ፡፡ “አንዴ ቆይ እስቲ እኔ የማወራው እኮ ስለ አዳማ ሆ/ል ነው የትኛወ ነው ኀይለማርያም ማሞ ሆ/ል”?.. ብሎ ቁጭ!.....የተሰበሰበው ሕዝብ ሳቀበት፡፡በሆታም የቀድሞ ስሙ ኃይለ-ማሪያም ማሞ መሆኑን ሕዝቡ ነገረው፡፡
ይህ ሰው ማ መሰላችሁ?>>>፣በቅርቡ በታማኝነቱ በፈንጂ ወረዳ ላይ የተመደበው -መላኩ ፈንታን ቀይሮ በግራ ተመላላሽ መስመር ላይ በአጥቂነት የሚጫወተው በከር ሻሌ ነው፡፡አሪፍ ነበር ይላሉ ፣አንዳንድ የአዳማ ነዋሪዎች በቁጭት፡፡ሳንጠቀምብት ተነጠቅን !... አንዳንዶች ውስጥ አዋቂዎች እንደሚሉት ሰውዬውን ለማስመለስ ሰልፍ ቢጤ የጠየቁ ሰዎች በመሃል አዳማ በየቀኑ በህቡዕ ፖሰታ ቤት አካባቢ ፈረንጆቹ ሲት ኢን(sit-in) የሚሉትን የሰላማዊ ተቃውሞ እያደረጉ መሆኑን ሲናገሩ ሰምቻለሁ፡፡ሰዎቹ ከንቲባችን ካልተመለሰ አንነሳም ድዳችንን ማስጣት ማንም አይከለክለንም-በገዛ ድድ ማስጫችን ማን ይከለክለናል ብለዋል፣ብለው ሲያወሩ ሰምቻለሁ ብሎ ነግሮኛል፡፡ካላመናችሁ ፖስታ ቤት አካባቢ ሂዱና እዩ…በዕርግጥ መፈክር አይዙም…በህቡዕ የሚደረግ ሰልፍ ነዋ…አችሉም እንዴ!
ናዝሬትዬ አትፍሩኝ በያቸው በናትሽ፣ግፋ ቢል ቀጨማ ነው!.....ግፋ ቢል አዱላላ ነው!.....ግፋ ቢል ሙክዬ ነው!...እነሆ አሁን ደግሞ መሪዎቿ በሚፈሯት ኣደማ/ናዘሬት የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ፅ/ቤትን ለመክፈት ተቸግረናል፡፡አንድነቶችጰዋጉሜ 3/2005ዓ/ም ባደረጉት የተቃውሞ ሰልፍ አስፈሪነታቸውን አሳዩ መሰለኝ ይኸው ዳፋው ለኛ ደረስን፡፡እሺ ከፍርኃት ሚገላግል ምን ይምጣ….አሃ!...ለምን እኛም እዛ ድድ ማስጫላይ ሲት ኢን አናደርግም….በቃ አደባባዩ ላይ እንገናኝ፡፡አደባባይ ማከራየት ተጀምሮ ይሆንደሞ እንዴ… ተከራይተንም ቢሆን ድምፃችንን ማሰማታችን አይቀርም፡፡
ተገናኘን ፡፡እንበርታ አቦ!

Comments

Popular posts from this blog

እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ

እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ የዓለም ሊቀ ሊቃውንት፣ የኪነ ጥበብ ምሑር የተከበሩ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ (ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም- ሚያዝያ ፪ ቀን ፳፻፬ ዓ/ም)፤ ‘’ኪነ ጥበብ የሰው ልጅን መንፈስ ለማዳበር፣ ሀገራችንን ለማሳደግ፣ ለማሳወቅ እና ለሕይወታዊ ኑሮ ተስፋ ለመፍጠር የላቀ ሚና ይጫወታል’’ ይላሉ። ለጥቀውም ‘’ዛሬ የምንሠራው ሥራ የዛሬን ሕይወት እያንጸባረቀ ለነገው ትውልድ ፈር መቅደድ አለበት፡፡” በሚል ስሜት ኪን ማንኛውንም የሰው ኑሮ ረገድ የሚነካ እንደሆነ ያስረግጣሉ። በዓለም የታወቁና የተከበሩት ኢትዮጵያዊ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በሰሜን ሸዋ በምትገኘው የሸዋ ነገሥታት ከተማ አንኮበር ላይ ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም ከአባታቸው አቶ ተክሌ ማሞ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ፈለቀች የማታወርቅ ተወለዱ። ገና በጨቅላ ዕድሜያቸው ፋሺስት ኢጣልያ ኢትዮጵያን በግፍ ሲወራት፣ የልጅነት ትዝታቸውም ይሄው የግፍ ወረራ እና ጦርነት የሚያስከትለው የሰው፣ የንብረት እና የባህል ጥፋት ፤ ከነጻነትም በኋላ ዐቢዩ ሥራ በወረራ የተበላሸችውን ሀገራቸውን እንደገና መገንባት እንደሆነ ነው። ለዚህም የሀገር ግንባታ አስፈላጊውን እውቀት መሸመት የፈለጉት በ ማዕድን ምሕንድስና ዘርፍ ነበር። ወላጆቻቸውና ዘመድ አዝማዶች ግን የኪነ ጥበብ ስጦታቸውን በቤታቸውና በከተማው ዙሪያ በሚስሏቸው ስዕሎች ተገንዝበውት ነበር። የመጀመሪያና መካከለኛ ትምህርታቸውን የት እና መቼ እንዳጠናቀቁ የተጻፈ መረጃ ባናገኝም፤ ገና በአሥራ አምስት ዓመታቸው በ ፲፱፻፵ ዓ/ም ለከፍተኛ ትምህርት ተመርጠው የምሕንድስና ትምህርታቸውን ለመከታተል ወደ እንግሊዝ አገር ይላካሉ። ተሰዳጅ ተማሪ ወጣቶቹ ንጉሠ ነገሥቱን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ሲሰናበቱ፣ አፈወርቅ ተክሌ ጃንሆይ የ...

Voice of Africa; empowering self esteem

(This post had been originally found on my other blog since May 25, 2013. Please consider post date while reading.)              As dreamed to have achieved the greatness of Africa every nation shall take part an adhesive self development of thinking, working, saving and serving. No desperate movement of individual, small group and, or clan interest shall be recorded in the coming Africa. African shall learn to really stand together.  Since the beginning, all the world noted    how potentially resourceful Africa was. The strong power of the western interest scrambled the continent for years and had employed varies tying techniques to lame the nation so that the invaders keep on sipping raw materials and human resources. As far as most African countries are concerned, ethnicity and poor administration have been playing a vital role in the sluggish growth of the continent in contrary to the fast emerging new techno...

የወሲብ ግፍና ዘመን

(This post had been on my other blog since April 04,2013. Please consider the original post date while reading.) ዘመነ ወሲብ ዛሬ ዛሬ መቼም ትዳር የሚባለው ጎጆ የጋብቻ   ምሰጢር ያለበት አልመስል ብሏል፡፡ በአፀያፊ መልኩ ዎንዶችና ሴቶች ገና ጨቅላ በሚባል የጉልምስና (በዘመንኛው ቃል የፍንዳታ እድሜ ይሉታል፡፡) እድሜያቸው ወሲብ መጀመራቸውና በአስራዎቹ አጋማሽ ላይ ሲደርሱ ዓለም ሰየጠንሁ  ያለበትን የወሲብ ክህሎት ጣራ ነክተው ከዚያ ሲዳክሩ ይከረሙና በወላጅ ይሁን በኑሮ ግፊት ትዳር ይመሰርታሉ፡፡ የዚህ አዲስ አይነት ጎጆ አባላት ደግሞ በአብዛኛው የሚያስቁ ጥነዶች የሆናሉ፡፡ እነዲህ ያለው ትዳር የተመሰረተው ለገንዘብ ወይም ለውጭ ሀገር ዕድል ከሆነ፤ ተጋቢዎቹም ሆነ ገገባው ሩቅ ሳይሄድ ህጋዊ ፍች እንደሚፈፀምበት ገና የሰርጉ እለት ያውቁታል፡፡ በቤተሰብ ግፊትና በአብሮ አበዶች ሆይሆይታ የሚቀለስም ተመሳሳይ ጎጆ አለ፡፡ ብቻ ይህኛውም መቼ  እነደሚሆን አይታወቅም እንጂ ላይዘልቅ እንደሚችል ተጋቢዎቹም ሆኑ እኛ ስለጋብቻው አሁን የሰማን ሰዎች ከልምዳችን በመነሳት እርግጠኞች መሆን ንችላለን፡፡ የሆኖሆኖ የዛሬ ትዳር ምነም እክሎችን የያዘ እነደሆነ ላሰታውሳችሁ፡፡ ውሽምና ድጋፍ ባያገኝም አስከዚህኛው ትውልድ በመዝለቁ፤ ወደሽርሙጥና  እና  የዳማ በሚል ስያሜ በቡድን ለሚፈፀም ሰው ሰራሽ አረመኔያዊ ወሲብነት አድጓ፡፡ ጥነዶች በአንድ ጣራ ስር ሆነው እንኳ በተመሳሳይ ሰዓት ከተለያዩ ሰዎች ጋር በስልክ ወሲብ ራሳቸውን ያረካሉ፡፡ የነውሩ ዘመን   በአባቶቻችንና ከዚያ ቀደም ባለው ትውልድ ወሲብ በይፋ በየመንገዱ እንደልብ የሚወሳ ሳይሆን እንደነውር ...