Skip to main content

ሰላም

ያቺ ጀግና እናቴ ስምንት ወንዶች ወልዳ፤

የሚጦራት አጣች፣

ረሃብ አንገላታት፣

ቁሩ ቀጭቶ አድምቶ፣

ማቅ አልባሷን ዘልቆ፣

እንዳልሆነ ሆነች፡፡

 

ያቺ ጀግና እናቴ ስምንት ወንዶች ወልዳ፤

ሁሉን ለጦር ማግዳ፤

በጉያዋ እሳት፣

እራሷን አንድዳ፣

በንዋየ ፍቅር፣ በስካረ ምንዳ፡፡

 

አይ እምይ እናቴ፤

ትረፊ ለሕይወቴ፤

ምንሽም መድሀኒት ነው፣

ይሽተተኝ በሞቴ፡፡

 

እንዳላገጡብን፣ እንደተላገዱ፤

እነርሱው ቆምረው፣

እነርሱው ሲሰጉ፤

ከጉጭን ወጥተው፣ ጎናችን ሲወጉ፤

ቀጠናውን አልፈው፣ አለምን ሲያሰጉ፤

ስንቀለብሰው፣ ጦርነቱን ባንዴ፤

መደቆሳቸውን፣ አምነው ዋጡት እንዴ?

 

አይ እምይ እናቴ፤

በእኛ እና በእነሱ፤

በአበረ እና አበሩ፤

ሽምቅና ክተት፤

መፍረስና አንድነት፤

በአንድነት ልዩነት፤

በሕበረብሔር ዜማ፤

ምናምን እያልን፤

ስምንቱም ልጆችሽ እየተዋደድን፤

እየተቋሰልን፤

እየተዋደቅን፤

ስርዝ ድልዝ ታሪክ፣

ቅርስ እንገነባለን፡፡

ተረኛ እስኪያፈርሰው፣ ዛሬም እንሰራለን፡፡

 

አንቺ ጀግና እናቴ፣ ስምንት ጊዜ ያማጥሽው፤

ታምር ሚስጥራቱን በማህፀን አዝለሽ፣

በእንግዴ ልጅ ስበብ፣

ቀብረሽ የሸሸግሽው፤

እስኪ አፍሽን ክፈች፣

ተናገሪው ይውጣ፤

እህህ እና እዬዬሽ፣

በንግግር ይንቃ፤

በውይይት ይድቃ፤

ነጠላ መዘቅዘቅ፣

ፊት መንጨትሽ ይብቃ፡፡

 

እምዬ እናት አለም ማህፀነ ለምለም፤

ከአረንጓዴው በቀር፣

ትዝ የሚለን የለም፤

ብለን እናውጋቸው ለልጅ ልጅ ልጆችሽ፤

ከእርግማኑ ያምልጡ ተባርከው በእጆሽ፡፡

 

አንቺ ጀግና እናቴ፣

ስምንት የወለድሽው፤

ስምንት የቀበርሽው፤

ስምንት ሺህ ሰላም ይወለድ በቤትሽ፤

ይለምልም፣ ይባረክ፣ ያፍራ ማህፀንሽ፡፡

 

ፀና ነጋሽ ታህሳስ 30/2014 ዓም.

Comments

Popular posts from this blog

እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ

እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ የዓለም ሊቀ ሊቃውንት፣ የኪነ ጥበብ ምሑር የተከበሩ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ (ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም- ሚያዝያ ፪ ቀን ፳፻፬ ዓ/ም)፤ ‘’ኪነ ጥበብ የሰው ልጅን መንፈስ ለማዳበር፣ ሀገራችንን ለማሳደግ፣ ለማሳወቅ እና ለሕይወታዊ ኑሮ ተስፋ ለመፍጠር የላቀ ሚና ይጫወታል’’ ይላሉ። ለጥቀውም ‘’ዛሬ የምንሠራው ሥራ የዛሬን ሕይወት እያንጸባረቀ ለነገው ትውልድ ፈር መቅደድ አለበት፡፡” በሚል ስሜት ኪን ማንኛውንም የሰው ኑሮ ረገድ የሚነካ እንደሆነ ያስረግጣሉ። በዓለም የታወቁና የተከበሩት ኢትዮጵያዊ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በሰሜን ሸዋ በምትገኘው የሸዋ ነገሥታት ከተማ አንኮበር ላይ ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም ከአባታቸው አቶ ተክሌ ማሞ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ፈለቀች የማታወርቅ ተወለዱ። ገና በጨቅላ ዕድሜያቸው ፋሺስት ኢጣልያ ኢትዮጵያን በግፍ ሲወራት፣ የልጅነት ትዝታቸውም ይሄው የግፍ ወረራ እና ጦርነት የሚያስከትለው የሰው፣ የንብረት እና የባህል ጥፋት ፤ ከነጻነትም በኋላ ዐቢዩ ሥራ በወረራ የተበላሸችውን ሀገራቸውን እንደገና መገንባት እንደሆነ ነው። ለዚህም የሀገር ግንባታ አስፈላጊውን እውቀት መሸመት የፈለጉት በ ማዕድን ምሕንድስና ዘርፍ ነበር። ወላጆቻቸውና ዘመድ አዝማዶች ግን የኪነ ጥበብ ስጦታቸውን በቤታቸውና በከተማው ዙሪያ በሚስሏቸው ስዕሎች ተገንዝበውት ነበር። የመጀመሪያና መካከለኛ ትምህርታቸውን የት እና መቼ እንዳጠናቀቁ የተጻፈ መረጃ ባናገኝም፤ ገና በአሥራ አምስት ዓመታቸው በ ፲፱፻፵ ዓ/ም ለከፍተኛ ትምህርት ተመርጠው የምሕንድስና ትምህርታቸውን ለመከታተል ወደ እንግሊዝ አገር ይላካሉ። ተሰዳጅ ተማሪ ወጣቶቹ ንጉሠ ነገሥቱን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ሲሰናበቱ፣ አፈወርቅ ተክሌ ጃንሆይ የ...

Voice of Africa; empowering self esteem

(This post had been originally found on my other blog since May 25, 2013. Please consider post date while reading.)              As dreamed to have achieved the greatness of Africa every nation shall take part an adhesive self development of thinking, working, saving and serving. No desperate movement of individual, small group and, or clan interest shall be recorded in the coming Africa. African shall learn to really stand together.  Since the beginning, all the world noted    how potentially resourceful Africa was. The strong power of the western interest scrambled the continent for years and had employed varies tying techniques to lame the nation so that the invaders keep on sipping raw materials and human resources. As far as most African countries are concerned, ethnicity and poor administration have been playing a vital role in the sluggish growth of the continent in contrary to the fast emerging new techno...

የወሲብ ግፍና ዘመን

(This post had been on my other blog since April 04,2013. Please consider the original post date while reading.) ዘመነ ወሲብ ዛሬ ዛሬ መቼም ትዳር የሚባለው ጎጆ የጋብቻ   ምሰጢር ያለበት አልመስል ብሏል፡፡ በአፀያፊ መልኩ ዎንዶችና ሴቶች ገና ጨቅላ በሚባል የጉልምስና (በዘመንኛው ቃል የፍንዳታ እድሜ ይሉታል፡፡) እድሜያቸው ወሲብ መጀመራቸውና በአስራዎቹ አጋማሽ ላይ ሲደርሱ ዓለም ሰየጠንሁ  ያለበትን የወሲብ ክህሎት ጣራ ነክተው ከዚያ ሲዳክሩ ይከረሙና በወላጅ ይሁን በኑሮ ግፊት ትዳር ይመሰርታሉ፡፡ የዚህ አዲስ አይነት ጎጆ አባላት ደግሞ በአብዛኛው የሚያስቁ ጥነዶች የሆናሉ፡፡ እነዲህ ያለው ትዳር የተመሰረተው ለገንዘብ ወይም ለውጭ ሀገር ዕድል ከሆነ፤ ተጋቢዎቹም ሆነ ገገባው ሩቅ ሳይሄድ ህጋዊ ፍች እንደሚፈፀምበት ገና የሰርጉ እለት ያውቁታል፡፡ በቤተሰብ ግፊትና በአብሮ አበዶች ሆይሆይታ የሚቀለስም ተመሳሳይ ጎጆ አለ፡፡ ብቻ ይህኛውም መቼ  እነደሚሆን አይታወቅም እንጂ ላይዘልቅ እንደሚችል ተጋቢዎቹም ሆኑ እኛ ስለጋብቻው አሁን የሰማን ሰዎች ከልምዳችን በመነሳት እርግጠኞች መሆን ንችላለን፡፡ የሆኖሆኖ የዛሬ ትዳር ምነም እክሎችን የያዘ እነደሆነ ላሰታውሳችሁ፡፡ ውሽምና ድጋፍ ባያገኝም አስከዚህኛው ትውልድ በመዝለቁ፤ ወደሽርሙጥና  እና  የዳማ በሚል ስያሜ በቡድን ለሚፈፀም ሰው ሰራሽ አረመኔያዊ ወሲብነት አድጓ፡፡ ጥነዶች በአንድ ጣራ ስር ሆነው እንኳ በተመሳሳይ ሰዓት ከተለያዩ ሰዎች ጋር በስልክ ወሲብ ራሳቸውን ያረካሉ፡፡ የነውሩ ዘመን   በአባቶቻችንና ከዚያ ቀደም ባለው ትውልድ ወሲብ በይፋ በየመንገዱ እንደልብ የሚወሳ ሳይሆን እንደነውር ...