Skip to main content

የመለስ ፋውነዴሽን (Meles Foundation)

(This post had been originally posted on April 03,2013 on my other blog please consider the original date)

በርካታ ባህላዊና ዘመናዊ መንግስታትን ያለ ግልፅ ቅኝ ተገዢነት ያስተናገደችው ሀገራችን ከጊዜ ወደ ጊዜ የመልካም አስተዳደር እጦትና የሰበዓዊ መብት ረገጣ እየተባባሰ በመምጣቱ ሳቢያ ሕዝቡ የዜግነት መብቱን በመንግስት ስልጣን ላይ ባሉ ግለሰቦች ወይንም ቡድኖች ፈቃድ ብቻ ሊሰጠው ወይም ሊነፈገው የሚችል መሆኑን እያመነ መጥቷል፡፡

ይባስ ብሎ መንግስት ለሕዝቡ ጥቅም በሚል በሚዘረጋቸው በማንኛውም የልማት መርሀ ግብሮች የመንግስትንና የግል ሌቦችን በሚያበረታታ መልኩ በዘፈቀደ አሰራር እየተሰራ ነገር ግን ለይስሙላ ያህል የሒሳብና የሚዲያ ሪፖርቶች እንደሚደረጉ ያደባባይ ሚስጥር ከሆነ እየሰነበተ ነው፡፡

የሆኖ ሆኖ ለሃያ አመታት፤ ሊያውም በዚህ በዘመነ ግሎባላይዜሽን ሀገራችንን በስልጣን ሲያስተዳድር የቆየው ኢሕአዴግ ከስልጣን ጊዜው ቀድሞ የክፉውን ጨለማ ሳይቀር አሸንፎ የመጣለትን ጠንካራ (በእኔ አተያይ አስሊ እና ከዱረዬ ባልተናነሰ በፈንግጪው ውጤት ተኮር) የሆነ መሪውን ካጣ ይኸው መንፈቅ ሞላው፡፡ ያለአንድ አምባገነን ምልክትነት ሕዝቡን ሰቅዞ ይዞ መምራት ያለመደበት የኢትዮጲያ መንግስት አገዛዝ ቀጣዩን መሪ አይነኬ አድርጎ በህዝቡ ላይ ለመሳል ተስኖት እየተውተተረተረ ይገኛል፡፡ ይህ በእንዲህ እነዳለም የመለስን ፋውነዴሽን ለማቋቋም ጥረቱ ቀጠሎ በመጪው ቅዳሜ በይፋ ፀድቆ ስራ ይጀምራል፡፡

የቅርቡን ቢልከሊነተንን ጨምሮ በርካታ የዓለም ሀገራት መሪዎች፤ ታዋቂ አረቲሰቶችና በየተለያዩ ስራቸው እውቅናና ሀብትን ያተረፉ የየዘርፉ ባለሙያዎች ራሳቸው እነደ አምባሳደር በመሆነን በርካታ የበጎ ፈቃድ ስራዎችን የሚሰሩ ድርጅቶችን አቋቁመው በአካባቢ ማህበራዊ እና ስነ-ምህዳራዊ ፋይዳዎችን ለማሻሻል ሲተጉ ይስተዋላል፡፡

ምንም እንኳ እኔ በግሌ የአቶ መለስ አድነናቂ ባልሆንም በረካታ የአፍሪካ፤የአውሮፓ፤ የእስያና የአሜሪካ ባለስልጣናትና ባለሀብት ወዳጆች እንደሚኖራቸው ግልፅ ነው፡፡ እንኳን ሙስና በተስፋፋበትና ሀገሪቱ በአንፃሩ የሰላም ችግር የሌለባት ጊዜ ለሃያ አንድ ዓመታት የመሩተ እሳቸው ይቅርና በፋሽስት ዘመን ወረራ የደረሰባቸው አፄ ኃ/ስላሴ እና በኢትዮጲያ የእርስ በእርስ ጦርነት ዘመን አምባገነን መሪ የሚል ስም የተለጠፈላቸው ጓድ መንግስቱ ኃ/ማሪያምም ቢሆኑ በመከራቸው ጊዜ ለሊሸሽጋቸው የሚችሉ ወዳጆችን በሹመት ዘመናቸው አፍርተው ነበር፡፡

ስለሆነም በአቶ መለስ ስም ለሚቋቋመው ፋውነዴሽን በረካታ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት ዜጎችና ድርጅቶች ገንዘባቸውን ሊሰጡና ፖለቲካዊ፤ ሐይማኖታዊ ወይም ሌላ ተፅዕኖ ለመፍጠር የሚችሉበትን መንገድ የበጁ እንደሆነ ጥረት ያደርጋሉ ብዬ አስባለሁ፡፡
ግና የዚህ ፋውንዴሽን ዓላማ የግለሰቡ መልካምነት መወደሻ መሆኑ ቀርቶ ለኢሕአዴግ መደነሻ፤ የልማት ሰራዎች አጋር መሆኑ ቀርቶ የተቀናቃኝ ፓረቲዎች መግረፊያ አሳር ከሆነ ፋውንዴሽንነቱ ይቀርና ይፈነደሳል፡፡

ነገር ግን የህ ፋውንዴሽን  አቶ መለስ ነበራቸው ተብሎ የሚታመንበትን ከፍተኛ የንባብ ልምድ ለተተኪው ትውልድ የሚያስተላልፍበትን ሰፊ ፐሮጀክተ የቀረፀና የሚሰራ ከሆነ፤ ሀይለቃልን ሳይቀር በበሰለ ቋንቋ እየተጠቀመ ተቀናቃኙን በትህትና መርታት የሚችል አንደበተ ርቱዕ ተናጋሪ ማፍራት የሚችልን መድረክ ካዘጋጀ፤ እንደቆሎ በተለቀመ እጅፅሁፍ አካሄዶችንና መመሪያዎችን መንደፍ ማዋቀርና ማብራራት የሚችሉ ፀሃፍትን የሚመለምልበት መንገድ ከቄሰ፤ እውነትም የሰውውን ስም ለዘመናት ማወደስ የሚችል ማዕከል የሆንና በሕይወት ዘመናቸው በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ወይም አቅም በማጣት ያከናወኗቸውን የግፍ ተግባራት ያሰተሰርይላቸዋል፡፡ 
ልናይ ኋላ ዶሮ “ለጄ ጭራም አትበላ፤” ብላለች አሉ፡፡

Comments

Popular posts from this blog

እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ

እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ የዓለም ሊቀ ሊቃውንት፣ የኪነ ጥበብ ምሑር የተከበሩ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ (ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም- ሚያዝያ ፪ ቀን ፳፻፬ ዓ/ም)፤ ‘’ኪነ ጥበብ የሰው ልጅን መንፈስ ለማዳበር፣ ሀገራችንን ለማሳደግ፣ ለማሳወቅ እና ለሕይወታዊ ኑሮ ተስፋ ለመፍጠር የላቀ ሚና ይጫወታል’’ ይላሉ። ለጥቀውም ‘’ዛሬ የምንሠራው ሥራ የዛሬን ሕይወት እያንጸባረቀ ለነገው ትውልድ ፈር መቅደድ አለበት፡፡” በሚል ስሜት ኪን ማንኛውንም የሰው ኑሮ ረገድ የሚነካ እንደሆነ ያስረግጣሉ። በዓለም የታወቁና የተከበሩት ኢትዮጵያዊ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በሰሜን ሸዋ በምትገኘው የሸዋ ነገሥታት ከተማ አንኮበር ላይ ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም ከአባታቸው አቶ ተክሌ ማሞ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ፈለቀች የማታወርቅ ተወለዱ። ገና በጨቅላ ዕድሜያቸው ፋሺስት ኢጣልያ ኢትዮጵያን በግፍ ሲወራት፣ የልጅነት ትዝታቸውም ይሄው የግፍ ወረራ እና ጦርነት የሚያስከትለው የሰው፣ የንብረት እና የባህል ጥፋት ፤ ከነጻነትም በኋላ ዐቢዩ ሥራ በወረራ የተበላሸችውን ሀገራቸውን እንደገና መገንባት እንደሆነ ነው። ለዚህም የሀገር ግንባታ አስፈላጊውን እውቀት መሸመት የፈለጉት በ ማዕድን ምሕንድስና ዘርፍ ነበር። ወላጆቻቸውና ዘመድ አዝማዶች ግን የኪነ ጥበብ ስጦታቸውን በቤታቸውና በከተማው ዙሪያ በሚስሏቸው ስዕሎች ተገንዝበውት ነበር። የመጀመሪያና መካከለኛ ትምህርታቸውን የት እና መቼ እንዳጠናቀቁ የተጻፈ መረጃ ባናገኝም፤ ገና በአሥራ አምስት ዓመታቸው በ ፲፱፻፵ ዓ/ም ለከፍተኛ ትምህርት ተመርጠው የምሕንድስና ትምህርታቸውን ለመከታተል ወደ እንግሊዝ አገር ይላካሉ። ተሰዳጅ ተማሪ ወጣቶቹ ንጉሠ ነገሥቱን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ሲሰናበቱ፣ አፈወርቅ ተክሌ ጃንሆይ የ...

Voice of Africa; empowering self esteem

(This post had been originally found on my other blog since May 25, 2013. Please consider post date while reading.)              As dreamed to have achieved the greatness of Africa every nation shall take part an adhesive self development of thinking, working, saving and serving. No desperate movement of individual, small group and, or clan interest shall be recorded in the coming Africa. African shall learn to really stand together.  Since the beginning, all the world noted    how potentially resourceful Africa was. The strong power of the western interest scrambled the continent for years and had employed varies tying techniques to lame the nation so that the invaders keep on sipping raw materials and human resources. As far as most African countries are concerned, ethnicity and poor administration have been playing a vital role in the sluggish growth of the continent in contrary to the fast emerging new techno...

የወሲብ ግፍና ዘመን

(This post had been on my other blog since April 04,2013. Please consider the original post date while reading.) ዘመነ ወሲብ ዛሬ ዛሬ መቼም ትዳር የሚባለው ጎጆ የጋብቻ   ምሰጢር ያለበት አልመስል ብሏል፡፡ በአፀያፊ መልኩ ዎንዶችና ሴቶች ገና ጨቅላ በሚባል የጉልምስና (በዘመንኛው ቃል የፍንዳታ እድሜ ይሉታል፡፡) እድሜያቸው ወሲብ መጀመራቸውና በአስራዎቹ አጋማሽ ላይ ሲደርሱ ዓለም ሰየጠንሁ  ያለበትን የወሲብ ክህሎት ጣራ ነክተው ከዚያ ሲዳክሩ ይከረሙና በወላጅ ይሁን በኑሮ ግፊት ትዳር ይመሰርታሉ፡፡ የዚህ አዲስ አይነት ጎጆ አባላት ደግሞ በአብዛኛው የሚያስቁ ጥነዶች የሆናሉ፡፡ እነዲህ ያለው ትዳር የተመሰረተው ለገንዘብ ወይም ለውጭ ሀገር ዕድል ከሆነ፤ ተጋቢዎቹም ሆነ ገገባው ሩቅ ሳይሄድ ህጋዊ ፍች እንደሚፈፀምበት ገና የሰርጉ እለት ያውቁታል፡፡ በቤተሰብ ግፊትና በአብሮ አበዶች ሆይሆይታ የሚቀለስም ተመሳሳይ ጎጆ አለ፡፡ ብቻ ይህኛውም መቼ  እነደሚሆን አይታወቅም እንጂ ላይዘልቅ እንደሚችል ተጋቢዎቹም ሆኑ እኛ ስለጋብቻው አሁን የሰማን ሰዎች ከልምዳችን በመነሳት እርግጠኞች መሆን ንችላለን፡፡ የሆኖሆኖ የዛሬ ትዳር ምነም እክሎችን የያዘ እነደሆነ ላሰታውሳችሁ፡፡ ውሽምና ድጋፍ ባያገኝም አስከዚህኛው ትውልድ በመዝለቁ፤ ወደሽርሙጥና  እና  የዳማ በሚል ስያሜ በቡድን ለሚፈፀም ሰው ሰራሽ አረመኔያዊ ወሲብነት አድጓ፡፡ ጥነዶች በአንድ ጣራ ስር ሆነው እንኳ በተመሳሳይ ሰዓት ከተለያዩ ሰዎች ጋር በስልክ ወሲብ ራሳቸውን ያረካሉ፡፡ የነውሩ ዘመን   በአባቶቻችንና ከዚያ ቀደም ባለው ትውልድ ወሲብ በይፋ በየመንገዱ እንደልብ የሚወሳ ሳይሆን እንደነውር ...