Skip to main content

የመለስ ፋውነዴሽን (Meles Foundation)

(This post had been originally posted on April 03,2013 on my other blog please consider the original date)

በርካታ ባህላዊና ዘመናዊ መንግስታትን ያለ ግልፅ ቅኝ ተገዢነት ያስተናገደችው ሀገራችን ከጊዜ ወደ ጊዜ የመልካም አስተዳደር እጦትና የሰበዓዊ መብት ረገጣ እየተባባሰ በመምጣቱ ሳቢያ ሕዝቡ የዜግነት መብቱን በመንግስት ስልጣን ላይ ባሉ ግለሰቦች ወይንም ቡድኖች ፈቃድ ብቻ ሊሰጠው ወይም ሊነፈገው የሚችል መሆኑን እያመነ መጥቷል፡፡

ይባስ ብሎ መንግስት ለሕዝቡ ጥቅም በሚል በሚዘረጋቸው በማንኛውም የልማት መርሀ ግብሮች የመንግስትንና የግል ሌቦችን በሚያበረታታ መልኩ በዘፈቀደ አሰራር እየተሰራ ነገር ግን ለይስሙላ ያህል የሒሳብና የሚዲያ ሪፖርቶች እንደሚደረጉ ያደባባይ ሚስጥር ከሆነ እየሰነበተ ነው፡፡

የሆኖ ሆኖ ለሃያ አመታት፤ ሊያውም በዚህ በዘመነ ግሎባላይዜሽን ሀገራችንን በስልጣን ሲያስተዳድር የቆየው ኢሕአዴግ ከስልጣን ጊዜው ቀድሞ የክፉውን ጨለማ ሳይቀር አሸንፎ የመጣለትን ጠንካራ (በእኔ አተያይ አስሊ እና ከዱረዬ ባልተናነሰ በፈንግጪው ውጤት ተኮር) የሆነ መሪውን ካጣ ይኸው መንፈቅ ሞላው፡፡ ያለአንድ አምባገነን ምልክትነት ሕዝቡን ሰቅዞ ይዞ መምራት ያለመደበት የኢትዮጲያ መንግስት አገዛዝ ቀጣዩን መሪ አይነኬ አድርጎ በህዝቡ ላይ ለመሳል ተስኖት እየተውተተረተረ ይገኛል፡፡ ይህ በእንዲህ እነዳለም የመለስን ፋውነዴሽን ለማቋቋም ጥረቱ ቀጠሎ በመጪው ቅዳሜ በይፋ ፀድቆ ስራ ይጀምራል፡፡

የቅርቡን ቢልከሊነተንን ጨምሮ በርካታ የዓለም ሀገራት መሪዎች፤ ታዋቂ አረቲሰቶችና በየተለያዩ ስራቸው እውቅናና ሀብትን ያተረፉ የየዘርፉ ባለሙያዎች ራሳቸው እነደ አምባሳደር በመሆነን በርካታ የበጎ ፈቃድ ስራዎችን የሚሰሩ ድርጅቶችን አቋቁመው በአካባቢ ማህበራዊ እና ስነ-ምህዳራዊ ፋይዳዎችን ለማሻሻል ሲተጉ ይስተዋላል፡፡

ምንም እንኳ እኔ በግሌ የአቶ መለስ አድነናቂ ባልሆንም በረካታ የአፍሪካ፤የአውሮፓ፤ የእስያና የአሜሪካ ባለስልጣናትና ባለሀብት ወዳጆች እንደሚኖራቸው ግልፅ ነው፡፡ እንኳን ሙስና በተስፋፋበትና ሀገሪቱ በአንፃሩ የሰላም ችግር የሌለባት ጊዜ ለሃያ አንድ ዓመታት የመሩተ እሳቸው ይቅርና በፋሽስት ዘመን ወረራ የደረሰባቸው አፄ ኃ/ስላሴ እና በኢትዮጲያ የእርስ በእርስ ጦርነት ዘመን አምባገነን መሪ የሚል ስም የተለጠፈላቸው ጓድ መንግስቱ ኃ/ማሪያምም ቢሆኑ በመከራቸው ጊዜ ለሊሸሽጋቸው የሚችሉ ወዳጆችን በሹመት ዘመናቸው አፍርተው ነበር፡፡

ስለሆነም በአቶ መለስ ስም ለሚቋቋመው ፋውነዴሽን በረካታ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት ዜጎችና ድርጅቶች ገንዘባቸውን ሊሰጡና ፖለቲካዊ፤ ሐይማኖታዊ ወይም ሌላ ተፅዕኖ ለመፍጠር የሚችሉበትን መንገድ የበጁ እንደሆነ ጥረት ያደርጋሉ ብዬ አስባለሁ፡፡
ግና የዚህ ፋውንዴሽን ዓላማ የግለሰቡ መልካምነት መወደሻ መሆኑ ቀርቶ ለኢሕአዴግ መደነሻ፤ የልማት ሰራዎች አጋር መሆኑ ቀርቶ የተቀናቃኝ ፓረቲዎች መግረፊያ አሳር ከሆነ ፋውንዴሽንነቱ ይቀርና ይፈነደሳል፡፡

ነገር ግን የህ ፋውንዴሽን  አቶ መለስ ነበራቸው ተብሎ የሚታመንበትን ከፍተኛ የንባብ ልምድ ለተተኪው ትውልድ የሚያስተላልፍበትን ሰፊ ፐሮጀክተ የቀረፀና የሚሰራ ከሆነ፤ ሀይለቃልን ሳይቀር በበሰለ ቋንቋ እየተጠቀመ ተቀናቃኙን በትህትና መርታት የሚችል አንደበተ ርቱዕ ተናጋሪ ማፍራት የሚችልን መድረክ ካዘጋጀ፤ እንደቆሎ በተለቀመ እጅፅሁፍ አካሄዶችንና መመሪያዎችን መንደፍ ማዋቀርና ማብራራት የሚችሉ ፀሃፍትን የሚመለምልበት መንገድ ከቄሰ፤ እውነትም የሰውውን ስም ለዘመናት ማወደስ የሚችል ማዕከል የሆንና በሕይወት ዘመናቸው በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ወይም አቅም በማጣት ያከናወኗቸውን የግፍ ተግባራት ያሰተሰርይላቸዋል፡፡ 
ልናይ ኋላ ዶሮ “ለጄ ጭራም አትበላ፤” ብላለች አሉ፡፡

Comments

Popular posts from this blog

Hino da Etiópia (voz) Ethiopia National Anthem (vocal) (source: http://s.ytimg.com)

The man who taught Mandela to be a soldier

       The man who taught Mandela to be a soldier By Penny Dale BBC Africa, Addis Ababa In July 1962, Col Fekadu Wakene taught South African political activist Nelson Mandela the tricks of guerrilla warfare - including how to plant explosives before slipping quietly away into the night. Mr Mandela was in Ethiopia, learning how to be the commander-in-chief of Umkhonto we Sizwe - the armed wing of the African National Congress (ANC). The group had announced its arrival at the end of 1961 by blowing-up electricity pylons in various places in South Africa. Then on 11 January 1962, Mr Mandela had secretly, and illegally, slipped out of South Africa. His mission was to meet as many African political leaders as possible and garner assistance for the ANC, including money and training for its military wing. And to be moulded into a soldier himself. During this trip, he visited Ethiopia twice and left a deep impression on those who met ...

እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ

እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ የዓለም ሊቀ ሊቃውንት፣ የኪነ ጥበብ ምሑር የተከበሩ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ (ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም- ሚያዝያ ፪ ቀን ፳፻፬ ዓ/ም)፤ ‘’ኪነ ጥበብ የሰው ልጅን መንፈስ ለማዳበር፣ ሀገራችንን ለማሳደግ፣ ለማሳወቅ እና ለሕይወታዊ ኑሮ ተስፋ ለመፍጠር የላቀ ሚና ይጫወታል’’ ይላሉ። ለጥቀውም ‘’ዛሬ የምንሠራው ሥራ የዛሬን ሕይወት እያንጸባረቀ ለነገው ትውልድ ፈር መቅደድ አለበት፡፡” በሚል ስሜት ኪን ማንኛውንም የሰው ኑሮ ረገድ የሚነካ እንደሆነ ያስረግጣሉ። በዓለም የታወቁና የተከበሩት ኢትዮጵያዊ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በሰሜን ሸዋ በምትገኘው የሸዋ ነገሥታት ከተማ አንኮበር ላይ ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም ከአባታቸው አቶ ተክሌ ማሞ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ፈለቀች የማታወርቅ ተወለዱ። ገና በጨቅላ ዕድሜያቸው ፋሺስት ኢጣልያ ኢትዮጵያን በግፍ ሲወራት፣ የልጅነት ትዝታቸውም ይሄው የግፍ ወረራ እና ጦርነት የሚያስከትለው የሰው፣ የንብረት እና የባህል ጥፋት ፤ ከነጻነትም በኋላ ዐቢዩ ሥራ በወረራ የተበላሸችውን ሀገራቸውን እንደገና መገንባት እንደሆነ ነው። ለዚህም የሀገር ግንባታ አስፈላጊውን እውቀት መሸመት የፈለጉት በ ማዕድን ምሕንድስና ዘርፍ ነበር። ወላጆቻቸውና ዘመድ አዝማዶች ግን የኪነ ጥበብ ስጦታቸውን በቤታቸውና በከተማው ዙሪያ በሚስሏቸው ስዕሎች ተገንዝበውት ነበር። የመጀመሪያና መካከለኛ ትምህርታቸውን የት እና መቼ እንዳጠናቀቁ የተጻፈ መረጃ ባናገኝም፤ ገና በአሥራ አምስት ዓመታቸው በ ፲፱፻፵ ዓ/ም ለከፍተኛ ትምህርት ተመርጠው የምሕንድስና ትምህርታቸውን ለመከታተል ወደ እንግሊዝ አገር ይላካሉ። ተሰዳጅ ተማሪ ወጣቶቹ ንጉሠ ነገሥቱን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ሲሰናበቱ፣ አፈወርቅ ተክሌ ጃንሆይ የ...