Skip to main content

አስተያየት ነውር ነውን? (Is a comment a taboo?)

(This post had been originally found on my other blog since April 14, 2013. Please consider the original date while reading.)

ስነ ሂስ ለለውጥ መርሃ ግብር መሰረታዊ አስተዋፅዖ ስለማድረጉ የጠቢባን እምነት ነው፡፡ ጠቢባንም የልፋታቸው ሚሰጥር ስለጥበብ ቋንቋና ምግባር እድገት ነው፡፡ በመሆኑም ጠቢባን ጥበበኛ የሚባሉት ባበረከቱት መሰረታዊና መደበኛ ያልሆኑ መልካም አስተዋፅዖዎች ነው፡፡
የፖለቲካ አመለካከት ቅኝት ከማጣቱ የተነሳ በእውቀት ማነስ ከሚወቃቀሱ፣ ከሚነካከሱ እና ከሚገዳደሉ የህዝብ አካላት ተፅዕኖ ምክኒትያት ሂስ መስጠትም ሆነ ግድፈትን ማውራት የተቃዋሚ ወይም ተፃራሪ ቦታን ስለሚያሰጥ ጤናማ የሚባል ወይም ለዕድገት የጋራ ሚና ያለው አስተያየት ማግኘት የለም፡፡ እሳት ወለደች አይነት ነው፡፡
ስለሆነነም ስለመፃህፍት፣ አስተምህሮ፣ የስልጠና ማዕከላት፣ የሆቴልና ቱሪዝም አገልግሎት፣ ወዘተ ባነሳን ቁጥር ስለዕድገትና ብልፅግና እያሰቡ ጉድለቶችን አንስቶ መተቸት ወይም ስህተቶችን መወረፍ እጅግ ነውረኛነትና “ከመልካም አሳቢው” ባለመፅሃፍ፣ አስተማሪ፣ የስልጠና ባለሙያ አልያም የሆቴልና ቱሪዝም አገልጋይ ዘንድ ጠላት ሆነኖ የመፈረጅን እድል ያጋፍጣል፡፡
ከዚህም ጋር ተያይዞ በሃገራችን እንጭጭ ሊባል የሚችል እድሜና እምብዛም አልተመደበለትም ሊባል የሚያስችል የገንዘብ በጀት የተደረገበትን የፊልም ጥበብን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሚቀርብበትን ትችት በመመርኮዝ ባለሙያዎችና ባለሃብቱ ጥለውት እየፈረጠጡ፤ መንግስትም በግብርና ተዛማጅ ማነቆ ጣጣዎች ከፍተኛ ጫና በማድረግ ስለጥበቡ መሻሻል ግድፈቶች እንዲሻሻሉ የጠቆሙ ሂሰኞችን ለማሳፈር በሚመስል አካሄድ ለዘርፉ ማደግ የራሳቸውን የእንቅፋትነት ድርሻ አየተወጡ ይገኛሉ፡፡
 ምንም እንኳ በኛ ሀገር የጥበብ፣ የገንዘብና የባለሙያ አቅም ማነስ የተነሳ ይሄ ነው ተብሎ የሚቆጠር ተውልድ ግብዐት ባይሆንም፤ ያለችውን ዘመን አከፋፍለው የሀገሪቱ ፊልም ከሙዚቃና ቴአትር ጥበብ እንደተወለደ ባሉዋቸው ውስን ማስረጃዎች ማጣቀሻነት ይከራከራሉ፡፡
የሆኖ ሆኖ የፊልምን መነሻ ሀሳብ ተረድቶ ከመተግበር አንፃር ገና ብዙ መሻሻል አለበት የሚሉ አስተያየቶች ከመበራከታቸውና የተለያዩ የፊልም ጥበብ ማሰልጠኛ ማዕከላት ብቅ ብቅ ከማለታቸው የሰሉ ብዕሮችም ገና ቦታ ቦታቸውን መያዝና እርምትን መጠቆም ከመጀመራቸው  በቋፍና በስግብግብነት በጥበቡ ዙሪያ እየተሳተፉ ያሉ ነጋዴዎችና አድር ባይ ጠቢባንን እንዲሁም ደንባራ የመንግስት አካላትን ወዳልተገባ እርምጃና እነቅስቃሴ ያስኳተናቸው ይዟል፡፡ 
ለመሆኑ አስተያየት መስጠት ነውር ነነው እንዴ? ከፊልም ጥበብ የሚገኙ ገንዘቦች መልሶ በይበቡ ዙሪያ ያሉ ሰዎችን ብቃት ለማሳደግና  ለፊልሙ ጥበብ የተሸለ ዋስትና እነዲኖር ማስቻልን የሚያበረታቱ አስተያየቶች ያልተጠበቀ የግብር ቁልል እንዲከተል፤ የፊልምና ቴእር መድረኮች በርከት ያሉ ያለስራ የሚቆዩበት ሰዓታት መኖራቸው በጥያቄ ምልክት መጠቆሙ በአስገዳጅ ሁኔታ የፖለቲካ ማራመጃ የውይይት መድረኮች እንዲሆኑ መገደድን ማስከተሉ ምን ያህል ትችትና አስተያየትዎ እዚህ ሀገር እርባና ቢስና እንደተፈለገ ተተርጉሞ ለራስ ውድቀት ጥቆማ መሆኑን የሚያስገነዝብ ነው፡፡
እኔ ስለማዳላለት የፊልም ሙያ ዘርፍ ጠቆምኩ እንጂ በሃገራችን ያሉ እንዲሻሻሉ አስተያየት የተሰጠባቸው በርካታ የስራና የንግድ ዘርፎች ሁሉ በመንግስትና በሌሎች “ተፅዕኖ መፍጠር” በሚችሉ ባለጊዜዎች ሚዛናዊ ያልሆነ ፍርድ እየተሰጠባቸውና እንደውግዝ እየተቆጠሩ የአገልግሎት ዘመናቸው እንዲያበቁ ተደርገው ተከታዩ ትውልድ እንዳይጠቀምባቸው ሆኗል፡፡ አሁንም ይህ ጉዳይ የፊልሙን ዘርፍ እያስፈራራው ይመስለኛልና ለሚመለከታቸው ሁሉ ይህን ጥያቄ አነሳለሁ፡፡ ለመሆኑ አስተያየት መስጠት ነውር ነው እንዴ?

Comments

Popular posts from this blog

Hino da Etiópia (voz) Ethiopia National Anthem (vocal) (source: http://s.ytimg.com)

The man who taught Mandela to be a soldier

       The man who taught Mandela to be a soldier By Penny Dale BBC Africa, Addis Ababa In July 1962, Col Fekadu Wakene taught South African political activist Nelson Mandela the tricks of guerrilla warfare - including how to plant explosives before slipping quietly away into the night. Mr Mandela was in Ethiopia, learning how to be the commander-in-chief of Umkhonto we Sizwe - the armed wing of the African National Congress (ANC). The group had announced its arrival at the end of 1961 by blowing-up electricity pylons in various places in South Africa. Then on 11 January 1962, Mr Mandela had secretly, and illegally, slipped out of South Africa. His mission was to meet as many African political leaders as possible and garner assistance for the ANC, including money and training for its military wing. And to be moulded into a soldier himself. During this trip, he visited Ethiopia twice and left a deep impression on those who met ...

እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ

እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ የዓለም ሊቀ ሊቃውንት፣ የኪነ ጥበብ ምሑር የተከበሩ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ (ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም- ሚያዝያ ፪ ቀን ፳፻፬ ዓ/ም)፤ ‘’ኪነ ጥበብ የሰው ልጅን መንፈስ ለማዳበር፣ ሀገራችንን ለማሳደግ፣ ለማሳወቅ እና ለሕይወታዊ ኑሮ ተስፋ ለመፍጠር የላቀ ሚና ይጫወታል’’ ይላሉ። ለጥቀውም ‘’ዛሬ የምንሠራው ሥራ የዛሬን ሕይወት እያንጸባረቀ ለነገው ትውልድ ፈር መቅደድ አለበት፡፡” በሚል ስሜት ኪን ማንኛውንም የሰው ኑሮ ረገድ የሚነካ እንደሆነ ያስረግጣሉ። በዓለም የታወቁና የተከበሩት ኢትዮጵያዊ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በሰሜን ሸዋ በምትገኘው የሸዋ ነገሥታት ከተማ አንኮበር ላይ ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም ከአባታቸው አቶ ተክሌ ማሞ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ፈለቀች የማታወርቅ ተወለዱ። ገና በጨቅላ ዕድሜያቸው ፋሺስት ኢጣልያ ኢትዮጵያን በግፍ ሲወራት፣ የልጅነት ትዝታቸውም ይሄው የግፍ ወረራ እና ጦርነት የሚያስከትለው የሰው፣ የንብረት እና የባህል ጥፋት ፤ ከነጻነትም በኋላ ዐቢዩ ሥራ በወረራ የተበላሸችውን ሀገራቸውን እንደገና መገንባት እንደሆነ ነው። ለዚህም የሀገር ግንባታ አስፈላጊውን እውቀት መሸመት የፈለጉት በ ማዕድን ምሕንድስና ዘርፍ ነበር። ወላጆቻቸውና ዘመድ አዝማዶች ግን የኪነ ጥበብ ስጦታቸውን በቤታቸውና በከተማው ዙሪያ በሚስሏቸው ስዕሎች ተገንዝበውት ነበር። የመጀመሪያና መካከለኛ ትምህርታቸውን የት እና መቼ እንዳጠናቀቁ የተጻፈ መረጃ ባናገኝም፤ ገና በአሥራ አምስት ዓመታቸው በ ፲፱፻፵ ዓ/ም ለከፍተኛ ትምህርት ተመርጠው የምሕንድስና ትምህርታቸውን ለመከታተል ወደ እንግሊዝ አገር ይላካሉ። ተሰዳጅ ተማሪ ወጣቶቹ ንጉሠ ነገሥቱን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ሲሰናበቱ፣ አፈወርቅ ተክሌ ጃንሆይ የ...