Skip to main content

Posts

ይብላኝ…

ችግር ወላፈኑ ጠብሶሽ በላብሽ ፍሳሽ ልታብሽው እንደዋዛ ካገር ወተሽ ደፋ ብለሽ ለቀረሽው በደሌን አሁን አወኩት ምትክ በሌለው ብዕርሽ ሰቆቃሽ ገፍቶ በፃፍሽው በድንጋይ ላይ ትርክትሽ በሞትሽ ቃል ገለፅሽው እህቴ ልናዘዝ ስሚኝ በባዕድ ሀገር ወርውሬ የገደልኩሽ እኔነኝ ስሚኝ… የጅብ ከሄደ ጩኸቴን የምፀት ቃል ምሬቴን የፍርሀት ጠርዝ መልክቴን የምላስ ተርፍ በረከቴን ይብላኝ… ያያትሽን ግብር ሳልፈፅም በሞቴ ሂወት ሳልሰጥሽ ከጠላትሽ ጋር አብሬ እኔው በጅ አዙር ገደልኩሽ ይብላኝ… የሞትሽ ፀፀት ሳይበቃኝ እንደገና ልገልሽ በሰልፍ ወደሞት ስቴጂ ዝም ብዬ ለማይሽ ይብላኝ… የሰው ትርፍ አርጌ እንደ አይረባ ለጣልኩት ውርደትሽን ክብር አርጌ በደምሽ ወዝ ለራስኩት የናቴ ልጅ… እኔን ይድፋኝ ልበልሽ ልደፋ ይድረሰኝ ፅዋሽ ነፃ ማውጣቱ ቢያቅተኝ ሞትሽን ባፌ ልጋራሽ /ፀደቀ ድጋፌ/

ሲሞት ያልገደለን…

     ሞቱን የገደለ አንድ ሰው ተገኘ ጭቆናን ረግጦ በልዕልና የናኘ     ሲታሰር   ያስፈታ ሲለቀቅ የፈታ     ሲሞት ያልገደለ ሲነሳ ይበረታ! ይልክልን ይሆን መንፈሱን መፅናኛ እምነቱን ፅናቱን ትዕግስቱን ስለእኛ አይጠረጠርም-ዛሬም ትላንትና መንፈሱ አብሮን አለ ሲያጀግን- ሲያፅናና የሮቢን ባህታዊ - እነሱ እነደሚሉን- የጥቁር ሰብዓዊ አካልን መንፈስን በአንድ አስተባብሮ ነፃነት ያወጀ በህገ-ተፈጥሮ ከኢየሱስ ቀጥሎ ሚስጥር የነገረን እውነትን በተግባር ቀምሶ ያስተማረን ማንዴላ ሕያው ነው በመኖሩ ያኖረን ሲሞት ያልገደለን፡፡ ተስፋዬ ዋቅቶላ 27/03/2006 ዓ/ም ናዝሬት-ኢትዮጵያ

የሷ ሱስ

የወደዷትን ልጅ እያወዳደሱ እያሞጋገሱ እንዲህ እያስደነሱ፤ ልፍታ ልተው ቢሏት እንኳንስ ፍቅሯና አይለቅህም ሱሱ! tsenawoo

ፍቅር በአርጩሜ!

ያኔ ትምህርት ቤት ቀለሙን ስንቀልም፣ ስሌት ስናሰላ ሰይንስ ስንጠበብ፣ አይናችን ሲገለጥ ሁሉን ስንካን፣ ፍቅርን ዝም አሉን የኛ መምህር፡፡ ትዝ ይለኛል ያኔ.... የክፍሌ ተማሪ ፍቅር ብታሲዘኝ፣ አይናፋርነጸቷ ዝምታዋ ቢያመኝ፣ ፍቅረሯ አያማለለ መማሩ ቢሳነኝ፣ ትዝ ይለኛል ያኔ.... ቃላት አውጣጥቼ ደብዳቤ መፃፌ፣ ባማሩ ቃላቶች ወደድኩሽ ማለቴ፤ ግና ምን ይሆናል.... ወድጃለሁ ብዬ ሃሳቤን በገለፅኩ፣ እሰልፉ መሃል ላይ ባርጩሜ ተገረፍኩ፡፡ መቼ በዚህ ብቻ.... እንደወንጀለኛ ፍርድ እንዳጎደለ፣ ማፍቀሬ ተወራ ጉድ እየተባለ፡፡ መቼ በዚህ ብቻ.... የአርጩሜው መዘዝ ስር አየሰደደ፣ ፍቅር በአርጩሜ ከኔ ተዋሀደ፡፡ ይመስገነው ዛሬ ሴትን አልጠይቅም፣ የማፍቀሩን ፀጋ ነፃነት አላውቅም፣ ሰጠየቅ እሺ እንጂ እኔ አልጠይቅም፡፡ እኔ!?.... ምን በወጣኝ! - እኔ አልጠይቅም፣ እኔ!?.... በስመአብ!! - እኔ አልጠይቅም፣ እኔ!?.... እማማ ትሙት - እኔ አልጠይቅም፡፡ 1981 ዓ.ም. — ናዝሬት በመስፍን ገብሬ ወንዳፍራሽ (ቅንጣት 2005 ዓ.ም.)

Model School 'Literature day' launched yesterday

On a recital of Artist Wogayehu Nigatu, the well known actor who made the Haddis Alemayehu 'Fikir Eskemekabir' live in the minds of all Ethiopian nationalists; mind it was on the date he was buried, Hidar 05, 19___; Mesfin Gebre has started a new literature stage where many young Ethiopian would learn to care for their art work. Mesfin Gebre, on his way to publicize his Poetry; 'Kintat', an Amharic poem book meaning a drop or fine,  has held an open day of the literature day in Adama/ Nazareth town. School of sadan has provided a regular stage to be hold every Thursday, 10:30-1:00 am, Ethiopian time.

'My nationality'

™û|Âá¿­Œ{...............( ፪ ) አደባባይ ቆሜ አላፊ አግዳሚ ሳይ ወሬ ጠኔ ይዞኝ ሟች ባገኝ ወይ ገዳይ፣ ወገን ባህር ማዶ ሲሰቃይ ‘ሰማለሁ እዚህ ለሆድ ቁርጠት፣ሲባትል አያለሁ ጉሮሮዬን ትቼ እኔ አገር እጠርጋለሁ የት እንዳለሁ ማወቅ ማመን ፈልጌያለሁ “ እህህ “ እሚል ባገኝ “ ለምን “ ልል ዝያለሁ ኮምቡጦር ስር ሆኜ በ “ ኢ “ ፣ በ “ ት “ ፣ በ “ ዮ “ …እጎለጉላለሁ፤፤ ወገኔን ታዘብኩት ላሯሯጠው ሲሮጥ አቅሉን እንደሳተ ህሊናው ሲናወጥ ሁሉን ሆዱ እስኪፈጅ ሁሉንም ተውኩለት፤ ይልቅ ጨከንኩና… ወሬ መፍጠር ባይችል እኔ ልፈጥርለት እሱ የራቀውን ኮረንቲ ያዝኩለት ራሴን በራሴ በእሳት ለኮስኩለት ለካስ በርዶት ኖሮ ተሰብስቦ ሞቆኝ ወሬዬን ኮምኩሞ እሳቴን አዳፍኖ፣ከነመፈጠሬ-ከነሞቴም ረሳኝ “ ኢትዮጵያዊነቴ “ ፣ የዚያን ጊዜ ገባኝ ከዚያች ቀን ጀምሮ ዜግነትም የለኝ ማነው ምፀተኛ የኔ ሰው የሚለኝ በሞቴ ሞቼለት በቁም ያልገደለኝ፡፡ (ለሰማዕቱ መምህር የኔሰው ገብሬ እና በሳዑዲ ፖሊሶች ለተገደሉ ሃበሾች፡፡) ©ተስፋዬ ዋ.2006 ዓ/ም                     ethopianwoo.blogspot.com

Yared Kebede, Cinematographer (Young pupil dressed culturally, taken from Holy Thrinity Cathedral school)